የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተግባር እያረጋገጠ ነው

Mar 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 10/2018 (ኢዜአ)፦ በከተሞች ተግባራዊ የተደረገው የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በተግባር እያረጋገጠ መሆኑን የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስቴር ገለጸ።

የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር በከተሞች ዜጎችን ተጠቃሚ ለማድረግ ብሎም የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ታስቦ የተቀረጸ ስትራቴጂካዊ ፕሮግራም ነው።

ከመርሃ ግብሩ ዋነኛ ዓላማዎችም መካከልም ዝቅተኛ ገቢ ያላቸውን ዜጎች መደገፍና የስራ ዕድል መፍጠር ተጠቃሾች ናቸው፡፡

በዚህም በርካታ ዜጎችን ከተረጂነት በማላቀቅ በየሶስት ዓመቱ በምርቃት ሂደት በማሳለፍ ሃብት ፈጣሪ እንዲሆኑ ማድረግ እያስቻለ ይገኛል።

የከተማና መሰረተ ልማት ሚኒስትር ዴኤታ ፈንታ ደጀን ለኢዜአ እንዳሉት፤ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት ከልማት መርሃ ግብር ጋር ተሰናስለው ተግባራዊ እየተደረጉ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብሩም በዝቅተኛ የኑሮ ደረጃ የሚገኙ ዜጎችን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት በማረጋገጥና ወደ ሃብት ፈጣሪነት በማሸጋገር ዘመናዊ የከተሜነት ምኅዳር እየፈጠረ መሆኑን ተናግረዋል።

የመርሃ ግብሩ ተጠቃሚ ዜጎችም በከተማ ፅዳትና የአረንጓዴ ውበት የሥራ ዕድል በማመቻቸት ለከተማ ነዋሪዎች ምቹ የአኗኗር ከባቢ መፍጠር ማስቻሉንም ገልጸዋል፡፡

በዚህም የከተሞችን ውበት ማስጠበቅ፣ ዘመናዊ የከተሜነት ምኅዳር ግንባታና በከተማ ግብርና ከፍተኛ አስተዋጽኦ እያበረከተ መሆኑን አስረድተዋል።

የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብሩ ከተጀመረ ወዲህ 1 ነጥብ 3 ሚሊዮን የሚሆኑ ዜጎች ሽግግር በማድረግ መቻላቸውን ተናግረዋል፡፡

በተያዘው የ2018 ዓ.ም በጀት ዓመት ባለፉት ወራት ውስጥ 380 ሺህ የከተማ ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር ተጠቃሚዎችን ሽግግር ማድረጋቸውን አስረድተዋል።

በሚቀጥሉት ሶስት ዓመታትም በከተሞች ልማታዊ ሴፍቲኔት መርሃ ግብር የታቀፉ ዜጎችን ተጠቃሚነት በማረጋገጥ ሙሉ በሙሉ ለማሸጋገር እንደሚሰራ አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026