የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

አዳዲስና የተከለሱ 79 የኢትዮጵያ ደረጃዎች ጸድቀዋል

Mar 24, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ መጋቢት 14/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት አዳዲስና የተከለሱ 79 ደረጃዎች መጽደቃቸውን ገለጸ።

አኒስቲትዩቱ በሰጠው መግለጫ እንዳስታወቀው፤ የደረጃዎች ቦርድ ካጸደቃቸው ደረጃዎች መካከል 56 አዳዲስ ሲሆኑ፤ 23 ደግሞ የተከለሱ ናቸው።

የደረጃዎች ቦርድ ደረጃዎችን ያጸደቀው በምግብና ግብርና ዘርፍ፣ በመሰረታዊና አጠቃላይ ዘርፍ እንዲሁም በኤሌክትሮ መካኒካል ዘርፍ መሆኑ ተመልክቷል።

የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር መሰረት በቀለ(ዶ/ር) በሰጡት መግለጫ፤ ቦርዱ ካጸደቃቸው ደረጃዎች መካከል አስገዳጅ የህጻናት ምግብ ደረጃዎች፣ የተከለሱ የህጻናት ምግብ መፈተሻዎች፣ አስገዳጅ የማርና ማር ውጤቶች ደረጃዎች፣ የማርና የማር ውጤት መፈተሻዎች ይገኙበታል ብለዋል።

የሳይበር ደህንነት አስገዳጅ ደረጃዎች እንዲሁም ሌሎች ደረጃዎች መጽደቃቸውንም ጨምረው ጠቅሰዋል።

የህጻናት ወተትን ጨምሮ ከውጭ የሚገቡ ምርቶች ጥራትና ደህንነትን በተገቢው መልኩ ለመፈተሽ፣ ወደ ውጭ የሚላኩ ምርቶች ጥራትና ተወዳዳሪነት በማሳደግ በኩል የደረጃዎቹ መጽደቅ ዘርፈ ብዙ ፋይዳ እንዳለው አብራርተዋል።

በአሁኑ ወቅት እንደ ሀገር ከ12ሺህ በላይ ደረጃዎች መኖራቸውን ጠቁመው፤ በደረጃዎች ቦርድ የጸደቁት ሥራ ላይ መዋል ተጨማሪ አቅም ይፈጥራሉ ብለዋል።

የአገልግሎት ጥራትን ማሳደግ ሌላው ዓላማ መሆኑን ጠቁመው፤ እንደ ሀገር ፋይዳው ከፍ ያለ መሆኑንም አስረድተዋል።


የኢትዮጵያ ደረጃዎች ኢኒስቲትዩት የሕዝብ ግንኙነትና ኮሙኒኬሽን ሥራ አስፈጻሚ ብሩክ ሀብቴ በበኩላቸው፤ በቦርዱ ከጸደቁት 79 ደረጃዎች ውስጥ 28ቱ አስገዳጅ መሆናቸውን ተናግረዋል።

በምግብና ግብርና ዘርፍ ስድስት የተከለሱ አስገዳጅ የግብርና ማዳበሪያ ደረጃዎች፣ ሁለት አስገዳጅ የህጻናት ምግብ ደረጃዎች፣ ሰባት የተከለሱ የህጻናት ምግብ መፈተሻዎች፣ አንድ የማርና ማር ውጤት ምርቶች አስገዳጅ ደረጃ፣ ሁለት አዲስ የማርና ማር ውጤት መፈተሻዎች ከጸደቁት መካከል እንደሚገኙበት አብራርተዋል።

በተመሳሳይም ሁለት አዲስ አጠቃላይ የምግብ ምርቶች አስገዳጅ ደረጃዎች፣ ሦስት አዲስ እና ዘጠኝ የተከለሱ በድምሩ 12 መፈተሻዎች መጽደቃቸውንም አንስተዋል።

በመሰረታዊና አጠቃላይ ዘርፍ ደግሞ ሦስት ጂኦግራፊያዊ መረጃ አስገዳጅ ደረጃዎች፣ አምስት አዲስ የሳይበር ደህንነት አስገዳጅ ደረጃዎች፣ 30 አዲስ የሳይበር ደህንነት መፈተሻዎች፣ ሁለት አዲስ የትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ አገልግሎትና አስተዳደር ሥርዓት አስገዳጅ ደረጃዎች በቦርዱ መጽደቃቸውን ተናግረዋል።

በኤሌክትሮ መካኒካል ዘርፍ ደግሞ ስድስት አዲስ የትራንስፖርት አስገዳጅ ደረጃዎችና አንድ አዲስ የባቡር መንገድ የምህንድስና አስገዳጅ ደረጃ እንደሚገኙበትም አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026