የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአስተዳደሩ የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እየተደረጉ ነው

Apr 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ድሬዳዋ፤ መጋቢት 29/2018 (ኢዜአ) ፡-በድሬዳዋ አስተዳደር የትንሳኤ በዓልን ምክንያት በማድረግ የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ ተደራሽ እየተደረጉ መሆናቸው ተገለጸ።

የትንሳኤ በአልን ምክንያት በማድረግ ከ50 በላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የተሳተፉበት የንግድ ኤግዚቢሽንና ባዛር ዛሬ በድሬዳዋ በይፋ ተከፍቷል።

የተዘጋጀውን ባዛር የከፈቱት የድሬደዋ አስተዳደር ከንቲባ ፅህፈት ቤት ኃላፊ አቶ ገበየሁ ጥላሁን፣ የስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊ አቶ ሮቤል ጌታቸው እና ሌሎች ከፍተኛ አመራሮች ናቸው።


በወቅቱም አቶ ሮቤል ጌታቸው እንዳሉት፤ የትንሳኤ በአልን ምክንያት በማድረግ የፍጆታ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ለማህበረሰቡ የማቅረብ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

በዛሬው ዕለት ምርትና ምርታማነታቸውን እያሳደጉ የሚገኙ ከ50 በላይ ሞዴል ኢንተርፕራይዞች የግብርናና የኢንዱስትሪ ምርቶች ለገበያ መቅረባቸውን ገልጸዋል።


በአለም ወቅታዊ ሁኔታ የተከሰተውን የንግድ እንቅስቃሴዎች መዛባት ተከትሎ የሚስተዋለውን የሸቀጦች ዋጋ ንረት ለመከላከል በሰንበት ገበያዎች ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ የማቅረብ ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።

ኤግዚቢሽኑና ባዛሩ ሸማቾችን ከሞዴል ኢንተርፕራይዞች ጋር በማገናኘት ዘላቂ የገበያ ትስስር እንዲፈጥሩ ማድረጉን አስረድተዋል።


በባዛሩ ላይ እየተሳተፉ የሚገኙ ሸማቾችና ሞዴል ኢንተርፕራይዞች በበኩላቸው የተዘጋጀው ባዛር የንግዱን ማህበረሰብ ከሸማቾች ጋር ያስተሳሰረ መሆኑን ለኢዜአ ገልጸዋል።

አቶ ኢዘዲን ሱልጣንና ወይዘሮ አስናቀች ፈንታ እንዳሉት፤ ምርቶችን ከመደበኛው የገበያ ዋጋ ባነሰ ማቅረባቸው ለሸማቾች አማራጭ ግብይት ለማካሄድ ያስችላቸዋል።

የአስተዳደሩ ንግድ ፅህፈት ቤት ከቢሮው ጋር በመቀናጀት በተለያዩ ቦታዎች የገበያ ስፍራዎችን በማዘጋጀት የገበያ የማረጋጋት ስራ መስራት እንዳለበትም አመልክተዋል።


በስፍራው ተገኝተው የተለያዩ ምርቶችን የሸመቱት ወይዘሮ የውብዳር አክሊሉ በአስተዳደሩ የተዘጋጀው ኤግዚቢሽንና ባዛር ሸማቾች በተመጣጣኝ ዋጋ ምርቶችን ለመሸመት እንዲችሉ ዕድል መፍጠሩን ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026