🔇Unmute
አዲስ አበባ፣መጋቢት 30/2018(ኢዜአ)፦በኦሮሚያ ክልል ለዘንድሮ የትንሳኤ በዓል ፍጆታ የሚውሉ መሰረታዊ ምርቶች በተሻለ ሁኔታ ለገበያ እንዲቀርቡ የክትትልና ቁጥጥር ስራ እየተሰራ መሆኑን የክልሉ ንግድ ቢሮ አስታወቀ።
በክልሉ ንግድ ቢሮ የገበያ ልማት ዳይሬክተር አቶ ጉቱ ተመስጌን ለኢዜአ እንደገለጹት፥ ለዘንድሮው የትንሳኤ በዓል የተሻለ የምርት አቅርቦት እንዲኖርና ህብረተሰቡ በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኝ ከባለድርሻ አካላት ጋር እቅድ በማውጣት የተለያዩ ተግባራት እየተሰሩ ነው።
በክልሉ በቂ ምርት ያለበት አከባቢና የዋጋ ሁኔታን በማጥናት ወደ ሌሎች የምርት አቅርቦት እጥረት ያለበት ቦታዎች እንዲደርስና የገበያ ትስስር ለመፍጠር ሰፊ ስራዎች መሰራታቸውን ተናግረዋል።
በተለይም አትክልትና ፍራፍሬ፣የቁም እንስሳት፣ እንቁላልና ዶሮ እንዲሁም ሌሎች በስፋት የሚቀርቡ የበዓል ፍጆታዎች መሆናቸውን ገልጸው፤ ዘይትና ስኳር ደግሞ በማህበራትና ዩኒየኖች በኩል እንዲቀርቡ ተደርገዋል ብለዋል።
ምርቶቹም በክልሉ ባሉት 775 የሰንበት ገበያዎችና በዐውደ ርዕይና ባዛሮች ላይ እየቀረቡ እንዳሉ የተናገሩት ዳይሬክተሩ፣በተለይም ሁለት ቀናት ብቻ የነበረው የሰንበት ገበያ ለበዓሉ ለ10 ተከታታይ ቃናት እንዲከፈት ተደርጓል ብለዋል።
ለበዓል ፍጆታ የሚውሉ በቂ መሰረታዊ ምርት እንዳለ የተናገሩት አቶ ጉቱ፣ አቅርቦቱን ለማሳለጥና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ እንዳይኖር የክትትልና ቁጥጥር ስራ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን አንስተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026