🔇Unmute
ጅማ ፤ሚያዝያ 3/2018 (አዜአ)፡-በጅማ ከተማ በዓሉን ምክንያት በማድረግ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ እና ምርቶችን በደበቁ የንግድ ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ መወሰዱን የከተማዋ ንግድ ፅህፈት ቤት አስታውቋል።
የጅማ ከተማ ንግድ ፅህፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ረውዳ ጀማል ለ ኢዜአ እንዳሉት፤ በዓሉን ምክንያት በማድረግ የተጋነነ እና ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ ባደረጉ እና ምርትን በደበቁ 24 የንግድ ተቋማት ላይ ህጋዊ እርምጃ ተወስዷል።
የፋሲካ በዓልን እና አንዳንድ ወቅታዊ ሁኔታን ተገን በማድረግ በሸቀጦች ላይ የዋጋ ጭማሪ በሚያደርጉ የንግድ ተቋማት ላይ የሚወሰደው ህጋዊ እርምጃ ተጠናክሮ ቀጥሏል ብለዋል።
የንግድ ተቋማቱ በከተማው ውስጥ በቂ ምርቶች እያሉ ምርትን በመደበቅ፣ በሸቀጦች ላይ ያልተገባ የዋጋ ጭማሪ በማድረግ እና ያለ ደረሰኝ በመሸጥ ህብረተሰቡን ለእንግልት የመዳረግ ህገወጥ ተግባር መፈጸማቸውን ጠቅሰዋል።
በዚህም 25 የንግድ ተቋማት እንዲታሸጉ እና ፍቃዳቸው እንዲነጠቅ ሲደረግ፣ ለ 17 የንግድ ተቋማት ደሞ ማስጠንቀቂያ መሰጠቱን አብራርተዋል።
በከተማዋ በቂ ምርቶች እና የበዓል ግብዓቶች እየቀረቡ ነው ያሉት ኃላፊዋ ህብረተሰቡ የግብዓት እጥረት ያለ በማስመሰል የዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ አካላትን ሲመለከት ጥቆማ እንዲሰጥም ጠይቀዋል።
የአለም አቀፍ ሁኔታዎችንም ሆነ የህዝብ በዓላትን ምክንያት በማድረግ የተጋነነ የሸቀጦች ዋጋ ጭማሪ የሚያደርጉ ህገወጥ ነጋዴዎች ላይ እየተወሰደ ያለው እርምጃ ተጠናክሮ እንደሚቀጥልም አረጋግጠዋል።
የንግዱ ማህበረሰብ አባላት ማህበረሰቡን በታማኝነት ሊያገለግሉት እንደሚገባ ኃላፊዋ አመልክተው ሸማቾችም መሰል ህገወጥ ተግባራትን ሲመለከቱ ለሚመለከተው የህግ አካል ጥቆማ እንዲሰጡም አሳስበዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026