የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የከተማዋ የአካባቢ ልማት ፕላን ቴክኖሎጂንና ፈጠራን በማስፋፋት የነዋሪዎችን ህይወት ለማሻሻል ያግዛል

Apr 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ሚያዝያ 20/2018(ኢዜአ)፦የአዳማ ከተማ የአካባቢ ልማት ፕላን ቴክኖሎጂንና ፈጠራን በማስፋፋት የነዋሪዎችን ሕይወት ለማሻሻል ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር የከተማዋ አስተዳደር ከንቲባ ሃይሉ ጀልዴ ገለፁ።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከኦሮሚያ ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት ጋር በመተባበር ያዘጋጀው የአካባቢ ልማት ፕላን ተፈፃሚነት ዙሪያ በየደረጃው ካሉ አመራሮችና ባለድርሻ አካላት ጋር ዛሬ መክሯል።

የአካባቢ ልማት ፕላን (Local Development Plan - LDP) በአንድ በተወሰነ የከተማ ክፍል ወይም መንደር ውስጥ የሚከናወኑ የልማት ስራዎችን፣ የመሬት አጠቃቀም እና የመሰረተ ልማት ዝርጋታን በዝርዝር የሚመራ የከተማ ፕላን አይነት ነው።

የአዳማ ከተማ አስተዳደር ከንቲባ ሃይሉ ጀልዴ እንደገለጹት፤ የከተማዋ የአካባቢ ልማት ፕላን ቴክኖሎጂንና ፈጠራን በማስፋፋት የነዋሪዎችን ህይወት ለማሻሻል ትልቅ አቅም የሚፈጥር ነው።

ፕላኑ መሬትን በአግባቡ ለማስተዳደርና ለማልማት ካለው ፋይዳ በተጨማሪ ለከተማ ግብርና፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራ፣ ለቴክኖሎጂ ልማትና ስማርት አዳማ ኢንሼቲቭ ለማሳካት ተጨማሪ አቅም መሆኑንም ተናግረዋል።

የከተማ ፕላኑ የነዋሪውን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄ ለመመለስ እንደሚያግዝም ገልጸዋል።

እንደ ከንቲባው ገለጻ፣ ፕላኑ ከዚህ በፊት የነበሩ የመልካም አስተዳደር እጦት ቅሬታዎችን፣ የመሬት አጠቃቀም ችግሮችና በመሰረተ ልማት ዝርጋታ ያሉ ማነቆዎችን በአግባቡ የፈተሸ ነው።


የኦሮሚያ ከተሞች ፕላን ኢንስቲትዩት ምክትል ዳይሬክተር አቶ ሸለመ አበበ በበኩላቸው፣ ፕላኑ አዳማ ከተማ ሪጂኦ ከተማ ሆና የተደራጀችበትን ዓላማ የሚያሳካ መሆኑን ተናግረዋል።

የከተማዋን መዋቅራዊ ፕላን በማዘጋጀት ለመስተዳድሩ በማስረከብ ወደ ትግበራ እንደተገባ ገልጸው፣ የአካባቢ ልማት ፕላን መዋቅራዊ ፕላኑን ውጤታማ ለማድረግ ፋይዳው የላቀ ነው ብለዋል።

የአዳማ ከተማን ዕድገትን ለማሳለጥ የተከናወኑ የኮሪደር ልማትና ሌሎች ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ መሰረተ ልማቶችን መሰረት በማድረግ መዋቅራዊ ፕላኑ መሰራቱንም ምክትል ዳይሬክተሩ ጠቁመዋል።

በክልሉ የአዳማ፣ የቢሾፍቱና የሻሸመኔ ከተሞች በሪጂኦ ማዕቀፍ ውስጥ ሆነው ወደ ልማት ሥራ መግባታቸውን አንስተው የጂማ፣ ማያ፣ ሮቤ እና ነቀምት ከተሞች መዋቅራዊና የአካባቢ ልማት ፕላኖችም እየተዘጋጁ መሆኑን ጠቅሰዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026