የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በአርብቶ አደር አካባቢዎች የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትል ለማረጋገጥ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሚና የላቀ ነው

May 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ፤ ሚያዝያ 24/2018(ኢዜአ)፦ በአርብቶ አደር አካባቢዎች የትምህርት ተደራሽነትና ጥራትል ለማረጋገጥ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ሚና የላቀ መሆኑ ተገለጸ።

’’አርብቶ አደሮችና ትምህርት’’ በሚል መሪ ሃሳብ 2ኛው ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስ ዛሬ በጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ አዘጋጅነት እየተካሄደ ነው።


በህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የሰው ሃብት ልማት፣ ስራ ስምሪትና የቴክኖሎጂ ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ ሰብሳቢ ነገሪ ሌንጮ (ዶ/ር) በኮንፍረንሱ እንደገለጹት፣ መንግስት ባለፉት የለውጥ ዓመታት ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ ልማትን ለማስፋፋት በሰራቸው ተግባራት ስኬቶች ተመዝግበዋል።

በቀጣይም የተጀመሩ ኢንሼቲቮችና ስኬቶችን ይበልጥ በማጠናከር ቀጣይነት ያለው ልማት ለማስመዝገብ በትኩረት እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በማህበራዊ ልማት በተለይም የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማረጋገጥ ከባለድርሻ አካላት ጋር በቅንጅት ሲሰራ መቆየቱን አስታውሰዋል።

በዚህ ረገድ የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት የሰው ኃይል ከማፍራት ጎን ለጎን ችግር ፈቺ የምርምር ሥራዎችን በማውጣት ለፖሊሲ ግብዓት እንዲውሉ ሲያከናውኑ የቆዩትን ስራዎች ማጎልበት እንዳለባቸው ጠቁመዋል።

የከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በተለይም በአርብቶ አደሮች አካባቢ ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት ለልማት እንዲውል በምርምር በማገዝ የአርብቶ አደሩ ሕይወት እንዲለወጥ በማድረግ በኩል የላቀ ሚና እንዳላቸው ተናግረዋል።

በተለይም የአርብቶ አደሩን የትምህርት ተደራሽነትና ጥራት ለማሳደግ የሚያግዙ ችግር ፈቺ የጥናትና ምርምር ስራዎችን ሊያጠናክሩ ይገባል ብለዋል።


የጋምቤላ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር ጋትሉዋክ ሮን (ዶ/ር) በበኩላቸው ዩኒቨርሲቲዎች የሰለጠነ የሰው ኃይል ከማፍራት ጎን ለጎን በአካባቢያቸው ያለውን እምቅ የተፈጥሮ ሃብት ወደ ልማት የሚቀየርበትን አቅም በምርምር እንዲያግዙ ጠይቀዋል።

ዛሬ የተጀመረው ሀገር አቀፍ የምርምር ኮንፍረንስም በቀጣይ ለሚወጡ ሀገራዊ የልማት ፖሊሲዎች ጠቃሚ ግብዓቶች ለማፍለቅ ያግዛል ብለዋል።


የጋምቤላ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ድሪባ ኢቲቻ (ዶ/ር) በዚሁ ጊዜ እንዳሉት ዩኒቨርሲቲው ከመማር ማስተማር ሥራው ጎን ለጎን የጥናትና ምርምር ስራዎችን በማከናወን የአካባቢው ማህበረሰብ ሕይወት እንዲለወጥ እየሰራ እንደሚገኝ ገልጸዋል።

በመድረኩ ዩኒቨርሲቲው በቀጣይ ለሚያከናውናቸው የጥናትና ምርምር ሥራዎች ተጨማሪ ግብዓቶችና ተሞክሮዎችን እንደሚያገኝም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026