🔇Unmute
አዲስ አበባ፣ሚያዝያ 27/2018 (ኢዜአ)፡-የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ የአገሪቱን ዘላቂ ዕድገትና የአረንጓዴ ኢኮኖሚ ግንባታን ማዕከል ባደረገ መልኩ እየተገነባ መሆኑ ተገለጸ፡፡
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) ካለፈው ሚያዝያ 25 ቀን 2018 ዓ.ም ጀምሮ እስከ ግንቦት 30 ቀን ድረስ የሚቆየውን የ"ኢትዮጵያ ታምርት" ኤክስፖ በይፋ መክፈታቸው ይታወቃል።
ጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ (ዶ/ር) በዚሁ ወቅት፤ በዘንድሮው “ኢትዮጵያ ታምርት” ኤክስፖ ላይ የሀገራዊ ርዕያችንን ተጨባጭ ስኬት መመልከት ትልቅ ክብር ነው ብለዋል።
ውጤት ተኮር አመራራችን ከዚህ ቀደም ታይቶ በማይታወቅ የኢንዱስትሪ መስፋፋት መንጸባረቁን ጠቅሰው ይኸውም የአምራች ኢንዱስትሪዎችን አማካይ የማምረት አቅም ከ47 በመቶ ወደ 67 በመቶ ከፍ ማድረግ መቻሉን ተናግረዋል፡፡
ባለፉት አራት አመታት ከ2ሺህ 800 በላይ የሀገር ውስጥ እና የውጭ ቀጥታ ኢንቨስትመንቶችን መሳብ መቻሉን ጠቅሰዋል፡፡
በዛሬው ዕለትም "በኢትዮጵያ የማኑፋክቸሪንግ ዘርፍ የአረንጓዴ ሽግግርን ማፋጠን፤መዋቅራዊ ለውጥን ከአየር ንብረት መቋቋም እና ከንግድ ተወዳዳሪነት ጋር ማጣጣም" በሚል መሪ ሐሳብ ውይይት ተካሂዷል፡፡
የአካባቢ ጥበቃ ባለስልጣን ምክትል ዋና ዳይሬክተር ፍሬነሽ መኩሪያ እንደገለጹት፤ በዘርፉ የአረንጓዴ ሽግግርን ለማፋጠንና የአየር ንብረት ለውጥን የሚቋቋም መዋቅራዊ ለውጥ ለማምጣት በትኩረት እየተሰራ ነው።
የኢንዱስትሪ ልማት የኃይል አቅርቦት በታዳሽ ኃይል ላይ የተመሰረተ መሆኑ ትልቅ ዕድል መሆኑን ጠቅሰው፥ ምርቶች ሲመረቱ የአፈር፣ የውሃ፣ የአየርና የድምጽ ብክለት እንዳያስከትሉ ጥብቅ ክትትልና ቁጥጥር እየተደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል፡፡
የማኑፋክቸሪንግ ዘርፉ ለሀገር የኢኮኖሚ ምሰሶ እንደመሆኑ መጠን፣ ከተፈጥሮና አካባቢ ጥበቃ ጋር ተስማምቶ መጓዝ ይገባዋል ብለዋል፡፡
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ ቢዝነስና ኢኮኖሚክስ ትምህርት ክፍል የመወያያ ጽሑፍ ያቀረቡት ተባባሪ ፕሮፌሰር ታደለ ፈረደ በበኩላቸው፥ ኢትዮጵያ የዘላቂ ልማት ግቦችን መሠረት አድርጋ እየሠራች መሆኑን ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ የተገነቡት ኢንዱስትሪ ፓርኮች ታዳሽ ኃይልን የሚጠቀሙ በመሆናቸው፣ ከብክለት የጸዳ ምርት እንዲመረትና ለአየር ንብረት የማይበገር የኢኮኖሚ ግንባታ ትልቅ መሠረት እንዲጣል አስችሏል ብለዋል።
ከአዲስ አበባ ዩኒቨርሲቲ የማኔጅመንት ትምህርት ክፍል የተሳተፉት ኢትዮጵያ ለገሰ (ዶ/ር) በበኩላቸው ኢትዮጵያ በታዳሽ ኃይል ላይ የምታደርገው ጥረት በቀጣይ የአረንጓዴ ማኑፋክቸሪንግ ማዕከል እንድትሆን ያስችላታል ብለዋል።
ምርቶቹ በታዳሽ ኃይል መመረታቸው በርካታ ፋይዳዎች እንደሚስገኝ ጠቅሰው በዋናነት በዓለም ገበያ ላይ ለሥነ-ምህዳር ተስማሚ የሆኑ ምርቶች ያላቸው ተፈላጊነት እየጨመረ በመሆኑ ኢትዮጵያ ተጠቃሚ ትሆናለች ብለዋል።
በተጨማሪም ከአፍሪካ አልፎ ወደ ተለያዩ የዓለም ገበያዎች በስፋት ለመግባትና ተወዳዳሪ ለመሆን እንደሚያግዝ ገልጸዋል።
#Ethiopian_News_Agency #ኢዜአ
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026