የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ ለኩታ ገጠም እርሻና የግብርና ሜካናይዜሽን ትኩረት በመስጠቱ ምርታማነታችንን እያሳደግን ነው

May 7, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

መቱ፤ ሚያዝያ 28/2018(ኢዜአ)፦ በኢሉአባቦር ዞን ለኩታ ገጠም እርሻና የግብርና ሜካናይዜሽን ትኩረት በመስጠቱ ምርታማነታቸውን ለማሳደግ እየሰሩ መሆናቸውን አርሶ አደሮች ተናገሩ።

የመኸር እርሻ ዝግጅትን አስመልክቶ ኢዜአ ያነጋገራቸው የዞኑ አርሶ አደሮች እንዳሉት የኩታ ገጠም እርሻና የግብርና ሜካናይዜሽንን በመተግበር ምርታማነታቸውን ለማሳደግ ወደ ስራ ገብተዋል።

የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በወቅቱ በመቅረቡ ማሳቸውን ደጋግመው በማረስና በማለስለስ በዘር ለመሸፈን እየሰሩ መሆናቸውንም ተናግረዋል።

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ የዞኑ አርሶ አደሮች መካከል አቶ ገረሙ በዛብህ በመኸር እርሻ በበኩታ ገጠም ለሚያለሙት መሬት የምርት ማሳደጊያ ግብዓት በወቅቱ በመቅረቡ የእርሻ ስራቸውን መጀመራቸውን ተናግረዋል።

ዘንድሮ በሰብል ልማት ምርታማነታቸውን ለመሳደግ የግብርና ሜካናይዜሽንና ኩታ ገጠም እርሻን በመጠቀም ለማልማት እየተዘጋጁ መሆናቸውን አንስተዋል።

ማዳበሪያና ምርጥ ዘር በወቅቱ መቅረቡ መሬታቸውን ደጋግመው በማረስ በዘር ለመሸፈን እንዳነሳሳቸው የተናገሩት ደግሞ በአሌ ወረዳ ነዋሪ አቶ ይርጋለም ጫሊ ናቸው።

ማሳቸውን በኩታ ገጠም ለማልማት በጋራ እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸው፣ ይህም ምርታማነታቸውን በመጨመር በኢኮኖሚ ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ተጨማሪ አቅም እንደሚሆናቸው ተናግረዋል።

በኩታ ገጠም የሚያለሙትን መሬት ከሌሎች አርሶ አደሮች ጋር በመሆን በትራክተር እያረሱ መሆናቸውን የገለጹት ደግሞ አበራ ተስፋዬ ናቸው።

ባለፉት ዓመታት ተግባራዊ ያደረጉት ኩታ ገጠም ልማት ኢኮኖሚያ ተጠቃሚነታቸውን ከጊዜ ወደ ጊዜ እያሳደገው መምጣቱንም ተናግረዋል።

በኢሉአባቦር ዞን በመኸር እርሻ 389 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለመሸፈን ታቅዶ ወደ ሥራ መገባቱን የገለጹት ደግሞ የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ አዳሙ ታከለ ናቸው።

በዞኑ ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ በተሰጠው ትኩረትም በመኸር እርሻ ከሚለማው መሬት 81 በመቶው በኩታ ገጠም እንደሚታረስ ተናግረዋል።

በዞኑ የግብርና ሜካናይዜሽን መስፋፋትን ተከትሎ የአርሶ አደሩ በትራክተር የማረስ ልምድ እያደገ መምጣቱን አንስተዋል።

በዞኑ በመኽር እርሻ ሩዝ፣ አኩሪ አተር፣ በቆሎ፣ ማሽላና ሌሎች ሰብሎች እንደሚለሙ ገልጸው፣ ለልማቱ የምርት ማሳደጊያ ግብአት በወቅቱ የማድረስ ሥራ እየተጠናቀቀ ነው ብልዋል።

በመኸር እርሻው ከ200 ሺህ በላይ አርሶ አደሮች፣ ማሕበራትና ባለሀብቶችን በማሳተፉ ከ15 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት ለመሰብሰብ ታቀዶ ወደ ሥራ መገባቱንም ጠቁመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026