የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

‎‎ስማርት ቆጣሪዎች ዘመናዊና ግልጽ አሰራርን በማስፈን የኃይል ብክነትን መቀነስ አስችለዋል

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ግንቦት 12/2018 (ኢዜአ) ፡-በሀገር አቀፍ ደረጃ የተጀመረው የስማርት ቆጣሪዎች ትግበራ ዘመናዊና ግልጽ አሰራርን በማስፈን የኃይል ብክነትን መቀነስ ማስቻሉን ‎የኢትዮጵያ ኤሌክትሪክ አገልግሎት አስታወቀ፡፡

በአገልግሎቱ የፖርትፎሊዮ ማኔጅመንት የዲስትሪዩብሽንና አውቶሜሽን ፕሮግራም ዳይሬክተር ተስፋዬ ሂርጳ ለኢዜአ እንዳሉት፤ አገልግሎቱ አስተማማኝ፣ቀልጣፋ እና ተደራሽ የኤሌክትሪክ አገልግሎት ለመስጠት የስማርት ቆጣሪዎችን ጨምሮ የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው፡፡

ለዚህም 500 ሺህ ስማርት ቆጣሪዎችን በመግዛት በሀገር አቀፍ ደረጃ እስካሁን 160 ሺህ ቆጣሪዎች ተገጥመው ሥራ መጀመራቸውን ገልጸዋል፡፡


ከተገጠሙት ስማርት ቆጣሪዎች መካከል 140 ሺህ ባለ ነጠላ፣ ቀሪዎቹ ደግሞ ባለ ሶስት ፌዝ መሆናቸውን ገልጸው፤ በቀጣይም ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡

አገልግሎቱን ይበልጥ ለማስፋት በቀጣይ 300 ሺህ የደረሱ ስማርት ቆጣሪዎች ወደ ሀገር ውስጥ እንደሚገቡ ገልጸዋል፡፡

ስማርት ቆጣሪዎች ደንበኞች ያለ አንዳች እንግልት ባሉበት ሆነው ክፍያ መፈጸም የሚያስችሉ ቴክኖሎጂዎች መሆናቸውን ተናግረዋል፡፡

ተጠቃሚዎች ምን ያህል ኃይል እየተጠቀሙ እንደሆነ እንዲረዱ ከማገዙም በላይ የኃይል አጠቃቀማቸውን ተረድተው አላስፈላጊ አጠቃቀምን በመቀነስ ኃይልን መቆጠብ ያስችላል ነው ያሉት።

ከቆጣሪና ከኃይል አጠቃቀም ጋር በተያያዘ የደንበኞችን ቅሬታ ሙሉ በሙሉ የሚያስቀር መሆኑን ገልጸው፤ በኃይል አጠቃቀም የመረጃ ንባብ መዘግየትና መሳሳት ተቋሙ ሊያጣ የሚችለውን ገንዘብ ያስቀራል ብለዋል፡፡

ስማርት ቆጣሪዎች ማናቸውንም አይነት የቆጣሪ ማጭበርበር ወይም ያልተፈቀደ ንክኪ በቀጥታ ወደ ማዕከላዊ ቁጥጥር ክፍሉ የማሳወቅ ብቃት እንዳላቸው ገልጸዋል፡፡

አገልግሎቱ የኃይል ሥርቆትን ለመከላከል የጀመረውን ሥራ የሚያግዝ መሆኑን ጠቅሰው፤ ከፍተኛ የኃይል ሥርጭት በሚያጋጥምበት ወቅት አደጋዎች እንዳይከሰቱ ለማድረግ ቆጣሪው ኃይል ማገድ የሚያስችል ስርዓት እንዳለው ጠቁመዋል።


በምሥራቅ አዲስ አበባ ሪጅን ኤሌክትሪክ አገልግሎት የቁጥር ስምንት አገልግሎት መስጫ ማዕከል ስራ አስኪያጅ ድሪባ አብዲሳ በበኩላቸው፤ማዕከሉ የነጠላና የባለሶስት ፌዝ ስማርት ቆጣሪዎችን ለነዋሪዎችና ለደንበኞች እየገጠመ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

የስማርት ቆጣሪዎች ቴክኖሎጂ አዲስ መሆኑን በመግለጽ፤ አገልግሎቱን በተመለከተ ለኅብረተሰቡ ሰፊ የግንዛቤ ማስጨበጫ ሥራዎች እየተከናወኑ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026