🔇Unmute
ሰመራ፣ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦የከሰም መስኖ ግድብ የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር፣የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ሊቀርፍ የቻለ ወሳኝ ፕሮጀክት መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) አስታወቁ።
የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) በተገኙበት ትናንት በይፋ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።
በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብረሃም(ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር።

ግድቡ ከዚህ ቀደም ይፈጥር ከነበረው የአደጋ ስጋት ተላቆ ለአካባቢው ነዋሪዎች አስተማማኝና ጠቃሚ የልማት መሠረተ-ልማት መሆን የቻለው በተደረገለት ስልታዊ የኢንጂነሪንግ ጥገናና ማሻሻያ አማካኝነት መሆኑን ገልጸዋል።
በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን የአደጋ ስጋት በመቅረፍ ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል ለተከናወነው የጥገናና ማሻሻያ ፕሮጀክትም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የከሰም መስኖ ግድብ የውሃ ፍሰት በተመጣጣኝና ቁጥጥር በተደረገበት ሁኔታ እንዲለቀቅ በማድረግ፣ ለአካባቢው የግብርና ሥራዎች ሙሉ በሙሉ አገልግሎት ላይ እንዲውል መደረጉን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እንዳሉት፥ ተጠግኖ ወደ አገልግሎት የገባው ግድቡ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው።
በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ይስተዋል የነበረውን ስጋት በማስወገድ ረገድ የተከናወነው ሥራ ውጤታማ መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የማህበረሰቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም ተናግረዋል።
ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...
May 20, 2026
ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...
Apr 24, 2026
ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...
Apr 22, 2026
አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...
Apr 15, 2026