🔇Unmute
ሰመራ፣ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦የከሰም መስኖ ግድብ የማሻሻያ ግንባታ መጠናቀቅ ከሚሰጠው ዘላቂ የልማት አገልግሎት ባሻገር፣የአካባቢውን ማህበረሰብ ለዓመታት ሲፈታተን የነበረውን የጎርፍ ስጋት ሊቀርፍ የቻለ ወሳኝ ፕሮጀክት መሆኑን የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብርሃም በላይ (ዶ/ር) አስታወቁ።
የከሰም መስኖ ግድብ የጥገና ማሻሻያ ፕሮጀክት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እና የመስኖና ቆላማ አካባቢዎች ሚኒስትር አብረሃም በላይ (ዶ/ር) በተገኙበት ትናንት በይፋ ተመርቆ ስራ ጀምሯል።
በዚህ ወቅት ሚኒስትር አብረሃም(ዶ/ር) እንዳሉት፥ የከሰም መስኖ ግድብ ቀደም ሲል በአካባቢው ማህበረሰብ ዘንድ እንደ ትልቅ ስጋት ይታይ ነበር።

ግድቡ ከዚህ ቀደም ይፈጥር ከነበረው የአደጋ ስጋት ተላቆ ለአካባቢው ነዋሪዎች አስተማማኝና ጠቃሚ የልማት መሠረተ-ልማት መሆን የቻለው በተደረገለት ስልታዊ የኢንጂነሪንግ ጥገናና ማሻሻያ አማካኝነት መሆኑን ገልጸዋል።
በአካባቢው ማህበረሰብ የነበረውን የአደጋ ስጋት በመቅረፍ ግድቡን ለታለመለት የመስኖ ልማት ለማዋል ለተከናወነው የጥገናና ማሻሻያ ፕሮጀክትም 2 ቢሊዮን ብር በጀት መውጣቱን ገልጸዋል።
በአሁኑ ወቅት የከሰም መስኖ ግድብ የውሃ ፍሰት በተመጣጣኝና ቁጥጥር በተደረገበት ሁኔታ እንዲለቀቅ በማድረግ፣ ለአካባቢው የግብርና ሥራዎች ሙሉ በሙሉ አገልግሎት ላይ እንዲውል መደረጉን ገልጸዋል።

በመርሃ ግብሩ ላይ የተገኙት የአፋር ክልል ርዕሰ መስተዳድር አወል አርባ እንዳሉት፥ ተጠግኖ ወደ አገልግሎት የገባው ግድቡ ህብረተሰቡን ከስጋት ያዳነ እና በርካታ ጥቅሞች ያሉት ነው።
በአካባቢው ነዋሪዎች ዘንድ ይስተዋል የነበረውን ስጋት በማስወገድ ረገድ የተከናወነው ሥራ ውጤታማ መሆኑን የጠቀሱት ርዕሰ መስተዳድሩ፤ የግድቡ ጥገና መጠናቀቅ የማህበረሰቡን የቆየ ጥያቄ የፈታ መሆኑንም ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026