የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

Apr 15, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት ቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ ገለጹ።

የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት የተመሰረተበትን 20ኛ ዓመት ምክንያት በማድረግ የከፍተኛ ባለሙያዎችና የሥራ ኃላፊዎች ውይይት እየተካሄደ ነው።

የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት (አግራ) የአነስተኛ አርሶ አደሮችን በግብዓትና በቴክኖሎጂ በመደገፍ የግብርና እድገትን ለማሳለጥ እንደ አውሮፓውያኑ ዘመን አቆጣጣር በ2006 የተመሰረተ አፍሪካ መር ተቋም ነው።


ተቋሙ የተሻሻለ የዘር ብዜትን፣ የአፈር ጤናማነትን በማስጠበቅና ለግብርና ምርቶችን የገበያ ዕድል በማመቻቸት ዘርፉን በማዘመን የምግብ ዋስትናን የማረጋገጥ ግብ ይዟል።

የኢትዮጵያ የቀድሞ ጠቅላይ ሚኒስትርና የአፍሪካ አረንጓዴ አብዮት ጥምረት ቦርድ ሊቀ መንበር ኃይለማርያም ደሳለኝ በዚህ ወቅት እንደተናገሩት፤ ግብርና ለአፍሪካ የምግብ ዋስትና እና የኢኮኖሚ ዕድገት ለማረጋገጥ የጀርባ አጥንት ነው።

አግራ ከ20 ዓመት በፊት ሲቋቋም ለአፍሪካ የስርዓተ ምግብ ዕጣ ፋንታ ወሳኝ የሆነውን ግብርና በማዘመን የዜጎችን ምርታማነት ለማሳደግ ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

ግብርና ለአፍሪካ ብልፅግና መሰረት መሆኑን ገልጸው፤ ለስኬታማነቱ የተቋማት ትብብርና ግልፅ የፖሊሲ አተገባበር ያስፈልጋል ብለዋል።

ኢትዮጵያ ባለፉት ዓመታት የግብርና ኤክስቴንሽን ስርዓት በማጠናከርና ቁርጠኛ አመራር በመስጠት ምርትና ምርታማነትን በማሻሻል የወጭ ንግዷን ማሳደግ መቻሏን ገልጸዋል።

በኢትዮጵያ ምርትና ምርታማነት እየጨመረ መምጣቱን ጠቅሰው፤ ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ለሌሎች የአፍሪካ ሀገሮች በምሳሌነት የሚጠቀስ ስኬት አስመዝግባለች ብለዋል።

ኢትዮጵያ በሰብል ልማት ብቻ ሳይሆን በእንስሳት ሀብት እና ሌሎች የግብርና ዘርፎች የአርሶ አደሮችን ተሳትፎ በማሳደግ በአህጉሪቷ ተጠቃሽ ለውጥ ማምጣቷን ገልጸዋል።

በአፍሪካ የግብርና ሽግግር በመፍጠር የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና ዘላቂ እድገትን ለማስፈን ለችግሮች መፍትሔ ማፈላለግ እንደሚገባም ተናግረዋል።

በአፍሪካ የምግብ ስርዓትን ብሔራዊ አጀንዳ ማድረግ ይገባል ያሉት የቦርዱ ሊቀ መንበር፤ አግራ የአፍሪካ ግብርና ሽግግር አቀጣጣይ ሆኖ እያገለገለ ነው ብለዋል።

አርሶ አደሩ ዘላቂ የአሰራር ስርዓት እንደሚፈልግ ገልጸው፤ ለሥርዓቱ ቀጣይነት ያለው የተቋማት ትብብር እንደሚያስፈልግ በአጽንኦት ገልጸዋል።

በአፍሪካ ህብረት የገጠር ልማት ክፍል እና የግብርናና ምግብ ዋስትና ዘርፍ ኃላፊ ጃኔት ኢደሜ (ዶ/ር)፤ ህብረቱ የምግብ ስርዓትን አሕጉራዊ አጀንዳ አድርጎ እየሰራ መሆኑን ገልጸዋል።


በአፍሪካ የግብርና ሽግግር ለመፍጠርና የማህበራዊ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትብብር መስራት ወሳኝ መሆኑን አንስተዋል።

የግብርና ሽግግር የኢኮኖሚ ዕድል ብቻ አይደለም ያሉት ኃላፊዋ፤ የደህንነትና ሉዓላዊነት ጉዳይ መሆኑን ገልጸዋል።

ለዚህ ደግሞ አካታች፣ ለአየር ንብረት ለውጥ የማይበገር፣ ጠንካራ ተቋማት መገንባትና የፖሊሲ ማዕቀፍ ማውጣት እንደሚገባ አመልክተዋል።

የአፍሪካን ትርክት በፈጠራና በጥምረት መገንባት እንደሚገባ ገልጸው፤ ታሪክ ያለፈ ብቻ ሳይሆን ነገን መገንባት ጭምር መሆኑን ተናግረዋል።

በቀጣይ 20 ዓመታት አርሶ አደሮችን በማጠናከር ግብርናን ለአፍሪካ ዘላቂ ዕድገትና ልማት መጠቀም እንደሚገባ አብራርተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026