የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

Jun 6, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ተጠቃሚ መሆናቸውን በአቮካዶ ምርት ማቅረብ ሥራ ላይ የተሰማሩ የአርሶ አደር ማህበራት ገለጹ።

በይርጋለም ኢንዱስትሪ ፓርክ ከሚንቀሳቀሱ 10 አምራች ኢንዱስትሪዎች አራቱ በአቮካዶ ዘይት ማምረት ሥራ ላይ የተሰማሩ ሲሆን ይህም ለአካባቢው አርሶ አደሮች የገበያ ትስስር በመፍጠር ተጠቃሚ እያደረጋቸው ነው።

በተለይም አርሶ አደሩ በሕብረት ሥራ ማህበራት ተደራጅቶ ምርቱን ለኢንዱስትሪዎች እንዲያቀርብ ምቹ ዕድል እየፈጠረ መጥቷል፡፡

አስተያየታቸውን ለኢዜአ ከሰጡ ማህበራት መካከል የ"ዶንጎራ ቀዋዶ አትክልትና ፍራፍሬ አምራችና አቅራቢ ማህበር" ሰብሳቢ አቶ ላታሞ ያዕቆብ እንደገለጹት፤ ማህበሩ በአምስት መሰረታዊ የሕብረት ሥራ ማህበራት በርካታ አርሶ አደሮችን አቅፎ የአቮካዶ ምርትን ለኢንዱስትሪዎች እያቀረበ ይገኛል።


ይህም ቀደም ሲል አርሶ አደሩ ገበያን በማፈላለግ ያጋጥመው የነበረውን የምርት፣ የጊዜና የጉልበት ብክነት በማስቀረት የተሻለ ተጠቃሚ እንዲሆን ማስቻሉን ተናግረዋል።

የማህበሩ አባላት የአቮካዶ ምርታቸውን በማህበሩ በኩል በቀጥታ ለኢንዱስትሪዎች በማቅረብ ገቢያቸውን እያሳደጉ መሆኑንም ገልጸዋል።

ሌላው የ”ፋያ ኢንተርፕራይዝ ማህበር” ሰብሳቢ ወጣት ሻላ ካሳ፤ በማህበር ተደራጅተው የአቮካዶ ምርትን በፓርኩ ውስጥ ለሚገኙ ኢንዱስትሪዎች በማቅረብ ተጠቃሚነታቸውን እያሳደጉ መምጣታቸውን ገልጿል።


በቀን ከ50 ሺህ እስከ 80 ሺህ ኪሎ ግራም የአቮካዶ ምርት ሰብስበው እንደሚያቀርቡ ገልጾ፣ በምርት አሰባሰብ ሂደት ለበርካታ ወጣቶች የሥራ ዕድል ተፈጥሯል ብሏል።

አሁን ላይ ገቢና ተጠቃሚነታቸው በከፍተኛ ሁኔታ ማደጉንም ተናግሯል።

የሲዳማ ክልል ኢንዱስትሪ ፓርኮች ልማት ኮርፖሬሽን ዋና ሥራ አስፈጻሚ አቶ ሀይሉ የተራ በበኩላቸው እንዳሉት፤ በአሁኑ ወቅት በፓርኩ በአቮካዶ ዘይት ለተሰማሩ አምራች ኢንዱስትሪዎች ተደራጅተው ምርት የሚያቀርቡ አርሶ አደሮች ተጠቃሚ እየሆኑ ነው።


ፓርኩ ወደሥራ ከገባ ያለፉት አምስት ዓመታት ከ83ሺህ ቶን በላይ የአቮካዶ ምርት ለፓርኩ መቅረቡን የጠቆሙት አቶ ሀይሉ፣ ለበርካቶች የሥራ ዕድል ለመፍጠር መቻሉንም ተናግረዋል።

በማህበር ተደራጅተው ለኢንዱስትሪዎቹ የአቮካዶ ምርት የሚያቀርቡ አርሶ አደሮችም ተጠቃሚ እየሆኑ ይገኛሉ ብለዋል።

አቶ ሀይሉ እንዳሉት በ43 ማህበራት የተደራጁ ከ132ሺህ በላይ አርሶ አደሮች ምርታቸውን ለፓርኩ በማቅረብ ተጠቃሚነታቸውን እያረጋገጡ ይገኛሉ፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በፓርኩ ለአቮካዶ ዘይት አምራች ኢንዱስትሪዎች ምርት የሚያቀርቡ ማህበራት ተጠቃሚ ሆነዋል

ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...

Jun 6, 2026

የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ ያነቃቃል

ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...

May 28, 2026

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026