የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ለመመለስ እየተከናወነ ያለው ተግባር ይጠናከራል-እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ግንቦት ፤ ግንቦት 12/2018(ኢዜአ)፦ ከለውጡ ወዲህ የህዝቡን የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎችን ለመመለስ እየተከናወነ ያለው ተግባር ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር) አስታወቁ።

የክልሉ እና የዞኑ ከፍተኛ አመራሮች በጉራጌ ዞን ከምሁር አክሊል ወረዳ ነዋሪዎች ጋር ህዝባዊ ውይይት አካሄደዋል።


በወቅቱም የማእከላዊ ኢትዮጵያ ክልል ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰው (ዶ/ር)፤ የክልሉ መንግስት ለህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ተገቢውን ምላሽ እየሰጠ መሆኑን አንስተዋል።

ለተነሱ የመሰረተ ልማት ጥያቄዎች ማህበረሰቡን ባሳተፈ አግባብ ምላሽ እንደሚሰጥም ርዕሰ መስተዳድሩ አመልክተዋል።

የወረዳውን የመስህብ ስፍራዎች እና ቅርሶች በአግባቡ በማልማትና በማስተዋወቅ የህዝቡን ተጠቃሚነት ለማሳደግ እንዲሁም የአገልግሎት ሰጪ ተቋማትን ለማስፋፋት ከባለሃብቶች ጋር በመቀናጀት እንደሚሰራም ገልጸዋል።


የምሁር ኢየሱስ ገዳም እና በዙሪያው ያሉ ቅርሶችን ለማልማት የተጀመሩ ስራዎችን ማጠናከር ከሁሉም እንደሚጠበቅ ተናግረዋል።

ባለሀብቶች በገዳሙ ዙሪያ የእንግዶች ማረፊያ በመገንባት ለዘርፉ እድገት አስተዋጽኦ እንዲያበረክቱም ጥሪ አቅርበዋል።

የጉራጌ ዞን ዋና አስተዳደሪ አቶ ላጫ ጋሩማ በበኩላቸው በአካባቢው፤ ያለውን ፀጋና ሀብት በመጠቀም የህብረተሰቡን ኑሮ በማሻሻል ተጠቃሚነቱን ለማረጋገጥ እየተከናወነ ያለው ተግባር ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል፡፡


ሰፋፊ ኢንቨስትመንቶችን በመሳብ ለወጣቶች የስራ እድል ፈጠራን የሚያሰፉ ኢንዱስትሪዎች ትኩረት እንደተሰጣቸው አመልክተዋል።

የወረዳው አስተዳዳሪ አቶ ብስራት ገብሩ በበኩላቸው ከለውጡ ወዲህ የአካባቢን ጸጋ በማልማት የህዝቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ ትኩረት መሰጠቱን ተናግረዋል።


በወረዳው የህዝብ ጥያቄዎችን ለመፍታት በንፁህ መጠጥ ውሃ፣ በጤና ዘርፍ በርካታ ተግባራት መከናወናቸውን ገልጸዋል።

በውይይት መደረኩ ላይ የተሳተፉ ከፍተኛ የክልሉና የዞኑ አመራሮች በዞኑ ምሁር አክሊል ወረዳ የሚገኘውን ታሪካዊው የምሁር እየሱስ ገዳምን ጎብኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026