የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በብሄረሰብ አስተዳደሩ የተገነቡ መሰረተ ልማቶች ህዝቡን ተጠቃሚ እያደረጉ ነው

May 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሰቆጣ፤ ግንቦት 13/2018 (ኢዜአ) ፦ በመንግስት የተገነቡ መሰረተ ልማቶች የህዝቡን ዘላቂ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እንዳስቻሉ የዋግ ኽምራ ብሄረሰብ አስተዳደር የመንገድ ትራንስፖርትና ሎጂስቲክስ መምሪያ አስታወቀ።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ በ33 ሚሊየን ብር በላይ ወጭ የተገነቡ የኮንክሪትና የተንጠልጣይ ድልድዮች ተመርቀው ለአገልግሎት ክፍት ተደርገዋል ።

በብሄረሰብ አስተዳደሩ በምክትል አስተዳዳሪ ማዕረግ የመንገድ ትራንስፖርትና ሎጀስቲክስ መምሪያ ኃላፊ አቶ ፀጋው እሸቴ እንደገለፁት ፤ መንግስት የአካባቢውን ማህበረሰብ በመሰረተ ልማት በማስተሳሰር ስኬታማ ስራዎችን እያከናወነ ነው።

በአሁኑ ወቅትም በ33 ሚሊዮን ብር ወጭ የተገነቡት በጋዝጊብላ ወረዳ የጎልሆ ወንዝ የኮንክሪት እንዲሁም የዝቋላ ወረዳ የጨዋ ተንጠልጣይ ድልድዮች መጠናቀቃቸውን አስረድተዋል።

የእነዚህ መሰረተ ልማቶች መጠናቀቅ የማሕበረሰቡን ትስስር የሚያጎለብቱ መሆኑን የገለጹ ሲሆን በክረምት ወቅት በሰው፣ በእንስሳትና ሌሎች ንብረቶች ላይ ይደርስ የነበረውን የጎርፍ አደጋ የሚያስቀር መሆኑን ገልጸዋል።

የጎልሆ ወንዝ የኮንክሪት ድልድይ ለስምንት ቀበሌዎች፤ የዝቋላ ወረዳ የጨዋ የተንጠልጣይ ድልድይ ደግሞ ለአራት ቀበሌዎች ክረምት ከበጋ አገልግሎት መስጠት የሚችሉ መሆኑን አንስተዋል።

በተጨማሪም በፌደራል መንግስት ወጭ እየተገነባ የሚገኘው የሰቆጣ -ላሊበላ-ጋሸና የአስፋልት መንገድ ግንባታ መንግስት ለመንገድ መሰረተ ልማት ዘርፍ የሰጠውን ትኩረት የሚያመላክት ነው ብለዋል።

ከዚህ በተጨማሪም የጤና፣ የትምህርት፣ የኤሌክትሪክ፣ የንጹህ መጠጥ ውሃና ሌሎች የልማት ፕሮጀክቶችን በመገንባት ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ የተከናወኑ ተግባራት ውጤታማ እንደሆኑም አስረድተዋል።

በአስተዳደሩ የጋዝጊብላ ወረዳ የመስቀሎ ቀበሌ ነዋሪ አቶ ሞላ ማሞ እንዳሉት፤ የጎልሆ ወንዝ ድልድይ ግንባታ ተጠናቆ ለአገልግሎት መብቃቱ ለአካባቢው ማሕበረሰብ እፎይታን የሰጠ ነው።

የድልድዩ መገንባት የክረምት ወቅት የሚከሰተውን የውሃ ሙላት በማስቀረት በተለይ የግብርና ምርቶችን ለማጓጓዝና ለገበያ ለማቅረብ እንዲሁም የኢንዱስትሪ ምርቶችን ወደ አካባቢው ለማስገባት እንደሚያስችልም ነው የተናገሩት።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ

ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...

May 20, 2026

በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ ቀርቧል  

ጅማ፤ ሚያዝያ 16/2018 (ኢዜአ)፡- በጅማ ዞን ባለፉት ዘጠኝ ወራት 52 ሺህ ቶን ቡና ለገበያ መቅረቡን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ቲጃኒ ተማም ተናገሩ...

Apr 24, 2026

የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂ የማጠናከር ተግባራት እየተከናወነ ነው

ጅግጅጋ፤ ሚያዝያ 13/2018 (ኢዜአ)፦ የኅብረት ሥራ ማኅበራትን በቴክኖሎጂና ሌሎች መስኮች የማጠናከር ሥራ እየተከናወነ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሠ መ...

Apr 22, 2026

ኢትዮጵያ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካውያን በምሳሌነት የሚጠቀስ ነው

አዲስ አበባ፤ሚያዝያ 6/2018(ኢዜአ)፡-ኢትዮጵያ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በስንዴ ልማት ያስመዘገበችው ስኬት ለአፍሪካዊያን በምሳሌነት የሚጠቀስ መሆኑን የአ...

Apr 15, 2026