🔇Unmute
መቱ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ):- በኦሮሚያ ክልል የእርሻ መሬትን ከማስፋፋት ባለፈ የግብርና ቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማጎልበት ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት መሰጠቱ ተገለጸ።
በኢሉአባቦር ዞን የመኸር አዝመራ በተጠናከረ መልኩ የቀጠለ ሲሆን በዛሬው ዕለት በዶረኒ ወረዳ የተዘጋጀ መሬት በበቆሎ ዘር የመሸፈን ስራ ተጀምሯል።

በዚሁ ጊዜ የኦሮሚያ ክልል መስኖና አርብቶ አደር ልማት ቢሮ ኃላፊ ኢንጂነር ግርማ ረጋሳ፤ በክልሉ የበጋና ክረምት እርሻ ስራ በስፋት እየተከናወነ ይገኛል ብለዋል።
በተለይም በክልሉ ባለፉት ጥቂት ዓመታት በመስኖ ልማት ስራ ትልቅ ውጤት መገኘቱን ጠቅሰው የአነስተኛ እና መለስተኛ መስኖ ልማት ግድቦች ግንባታ መጠናከሩንም ገልጸዋል።
የምግብ ዋስትናን ማረጋገጥ የሚቻለው በዋናነት ግብርናን በማስፋፋት መሆኑን የገለጹት ኢንጂነር ግርማ፣ በበጋ ስንዴ ልማት በክልሉ ትልቅ ስኬት መመዝገቡን አስታውሰዋል።
ይህም ቀድሞ የነበረውን በዓመት አንዴ የማምረት ባህል በማሻሻል፣ ለክረምት እርሻው ተጨማሪ ትልቅ አቅም መፍጠሩን ገልጸዋል።
በተያዘው የመኸር አዝመራም ለግብርና ልማት መዋል የሚችለውን መሬት አሟጦ በማረስ እና የግብርና ሜካናይዜሽንን በመጠቀም ምርታማነትን ለማሳደግ ትኩረት ተደርጓል ብለዋል።

በኢሉአባቦር ዞን በክረምት እርሻ 389 ሺህ ሄክታር መሬት በተለያዩ የሰብል ዓይነቶች ለመሸፈን እየተሰራ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዞኑ ዋና አስተዳዳሪ አቶ እንዳልካቸው ተፈሪ ናቸው።
በዞኑ ወረዳዎች የኩታ ገጠም እርሻዎችን በዘር የመሸፈን ስራ ተጠናክሮ መቀጠሉንም አንስተዋል።
በሁሉም ወረዳዎች ምርታማነትን የሚያሳድግ የግብርና ሜካናይዜሽን አቅርቦት እያደገ መምጣቱን የጠቀሱት ዋና አስተዳዳሪው፣ የክረምት እርሻው በትራክተር በመታገዝ እንዲታረስ ትኩረት መሰጠቱን አክለዋል።

የዶረኒ ወረዳ ግብርና ልማትና መሬት አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ለሊሴ አመና በበኩላቸው፣ በወረዳው በክረምት እርሻ ከ17 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ ሰብሎች የማልማት ስራ እየተከናወነ መሆኑን አስታውቀዋል።
በዚህም በተለይ የበቆሎ ምርትን በእጥፍ ለማሳደግ መታቀዱን ገልጸዋል።
በክረምት እርሻው ላይ የተሰማሩ የወረዳው አርሶ አደሮችም፣ የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ ከሚረዱ ሰብሎች ጎን ለጎን ከፍተኛ የኢኮኖሚ ጠቀሜታ ያላቸውን ሰብሎችም በትኩረት እንደሚያመርቱ ተናግረዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026