የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን ለህብረተሰቡ ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት መስጠት አስችሏል

Jun 8, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ግንቦት 30/2018 (ኢዜአ)፡-የአዲስ አበባ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን ምቹና ቀልጣፋ አገልግሎት ማግኘት እንዳስቻላቸው ተጠቃሚዎች ገለጹ፡፡

መንግስት በትራንስፖርት ዘርፉ ላይ እያደረጋቸው ያሉ ሁለንተናዊ ማሻሻያዎችና በመዲናዋ የተገነቡት ዘመናዊ የአውቶብስ ፌርማታዎች ለአገልግሎቱ መቀላጠፍና ለተሳፋሪዎች ምቾት የጎላ አስተዋጽኦ እያበረከቱ ነው፡፡

በመዲናዋ ደረጃቸውን በጠበቁና ዘመናዊ ተሽከርካሪዎች ለማህበረሰቡ የተሳለጠ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት ገቢራዊ ተደርጓል፡፡

በአዲስ አበባና በዙሪያዋ በሚገኙ ከተሞች ሳምንቱን ሙሉ ያለማቋረጥ የትራንስፖርት አገልግሎት በማቅረብ ላይ ያሉት የከተማ አውቶብሶች ለነዋሪዎች ኢኮኖሚዊና ማህበራዊ እፎይታን እየሰጡ ይገኛሉ፡፡

የአገልግሎቱ ተጠቃሚ የሆኑት አቶ መኮንን ለገሰ ለኢዜአ እንዳሉት፤ የብዙሃን ትራንስፖርት ከሌሎች አማራጮች አንጻር አነስተኛ ታሪፍ ያለው በመሆኑ ዝቅተኛ ገቢ ላላቸው የህብረተሰብ ክፍሎች ትልቅ አቅም ይፈጥራል፡፡

የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት በተቀመጠላቸው የጊዜ ሰሌዳ የሚንቀሳቀሱ መሆናቸውን ገልጸው፤ ይሄውም ያለ ምንም እንግልት በሰዓታቸው የሥራ ቦታቸው ላይ እንዲገኙ እንዳስቻላቸው ተናግረዋል፡፡

ገቢያቸውን ያማከለና ተመጣጣኝ የትራንስፖርት አገልግሎት ከማግኘት ባለፈ ለሥራቸው መቃናትና ምርታማነት የጎላ አበርክቶ እንዳለው ጠቅሰዋል፡፡


ሌላኛዋ አስተያየት ሰጭ ወይዘሮ መስከረም ዳመነ፤ አገልግሎቱ በየጊዜው እየተሻሻለ በመምጣቱ ጠዋትም ሆነ ማታ ፈጣን፣ ምቹና ቀልጣፋ ግልጋሎት እያገኙ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን የነዋሪዎች የዕለት ከዕለት እንቅስቃሴ በማሳለጥ ገንቢ አስተዋጽኦ እያደረገ ነው ብለዋል፡፡

የከተማ አውቶብስ አሽከርካሪዎች በበኩላቸው ቴክኖሎጂን መሠረት ያደረገው አዲሱ አሠራር በሥራቸው ላይ ትልቅ መነቃቃት መፍጠሩን ተናግረዋል፡፡


አቶ ያለው ነጋ በትራንስፖርት ዘርፉ የተተገበረው ሪፎርም በካሜራና ጂፒኤስ (GPS) የታገዘ ዘመናዊ አሰራርን በማምጣት የአሽከርካሪዎችን የቴክኖሎጂ አቅም ማሳደጉን ገልጸዋል፡፡

ቴክኖሎጂው ቀደም ሲል በፌርማታዎች ይስተዋሉ የነበሩትን ሰልፎች በማስቀረት በመዲናዋና ከዙሪያ ከተሞች ለሚመጡ ተጠቃሚዎች ተመራጭ መሆኑን ተናግረዋል፡፡


ሌላኛዋ አሽከርካሪ ወይዘሮ ፍሬህይወት ኤካ፤ የብዙሃን ትራንስፖርት አገልግሎት መዘመን በተለይ ርቀት ላላቸው መስመሮች ከታሪፍ አንፃር እጅግ አዋጭ ነው ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026