🔇Unmute
ሮቤ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በከፍተኛ ትምህርት ተቋማት የሚከናወኑ የምርምር ሥራዎች ችግር ፈቺ፣ ውጤታማና ወጥ አሠራር እንዲኖራቸው በማድረግ፣ ለሀገራዊ የልማት ዕቅድ መሳካት የድርሻቸውን እንዲወጡ የተጀመሩ ሥራዎች እንደሚጠናከሩ የትምህርት ሚኒስቴር አስታወቀ።
መደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ለተመራማሪዎችና ለመምህራን በዘመናዊ የምርምር ማሻሻያ ስትራቴጂዎችና ተያያዥ ጉዳዮች ላይ ያተኮረ የአቅም ግንባታ ሥልጠና መስጠት ጀምሯል።

በትምህርት ሚኒስቴር የምርምርና ማኅበረሰብ ጉድኝት ሥራ አስፈጻሚ ሰራዊት ሐንድሶ (ዶ/ር) በሥልጠናው መክፈቻ ላይ እንደገለጹት፤ ዩኒቨርሲቲዎች ከመማር ማስተማር በተጓዳኝ ችግር ፈቺ የምርምር ሥራዎችን እያካሄዱ ይገኛሉ።
"የሀገራት ዕድገት ዋና ምስጢር ጥራት ያለው የምርምርና የፈጠራ ሥራዎች ውጤት ነው" ያሉት ሥራ አስፈጻሚው፤ ዩኒቨርሲቲዎች ከአካባቢያቸው ባለፈ ለሀገሪቱ የልማት ግብ መሳካት የበኩላቸውን አስተዋፅኦ ማበርከት አለባቸው ብለዋል።
ሥልጠናውም ምሁራን በየጊዜው ከሚለዋወጡ ዓለም አቀፋዊ የምርምር ስልቶች ጋር እንዲራመዱ ለማስቻል ያለመ መሆኑን ገልጸዋል።

የመደ ወላቡ ዩኒቨርሲቲ ፕሬዚዳንት ብርሃነመስቀል ጠና (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ተቋሙ ጥራት ያለው ሥልጠና ከመስጠት ጎን ለጎን የተጀመረውን ሀገራዊ ልማት ለመደገፍ እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።
ዩኒቨርሲቲው በበጀት ዓመቱ በትኩረት እየሠራባቸው ከሚገኙ ዋና ዋና የምርምር ዘርፎች መካከል ግብርና፣ ዘላቂ የተፈጥሮ ሀብት ጥበቃ፣ ጤና እና ቱሪዝም ተጠቃሽ ናቸው ብለዋል።
ፕሬዚዳንቱ አክለውም፣ ቀደም ሲል በተናጠል ይሰሩ የነበሩ የምርምር ሥራዎችን በማቀናጀት፣ የተሻለ ተፅዕኖ መፍጠር የሚችሉ ግዙፍ የምርምርና የፕሮጀክት ሥራዎች እየተከናወኑ መሆኑንና ሥልጠናውም ትልቅ አቅም እንደሚሆን አመልክተዋል።
የዩኒቨርሲቲው የአካዳሚክና ምርምር ጉዳዮች ምክትል ፕሬዚዳንት በዛብህ ወንድሙ (ዶ/ር)፤ ይህ ዓይነቱ ሥልጠና በጀትን በቁጠባ በመጠቀም ተወዳዳሪና ተፅዕኖ ፈጣሪ የምርምር ውጤቶችን ለማፍራት የሰው ኃይል አቅምን እንደሚገነባ ገልጸዋል።

ሥልጠናው በተለይም በመሠረታዊ የምርምር ሥርዓትና በምርምር ሥነ-ምግባር፣ በሰው ሠራሽ አስተውሎት አጠቃቀም፣ በምርምር ፈንድ አፈላለግ ስልቶች ላይ ያተኮረ ነው ብለዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026