🔇Unmute
መቱ፣ ሰኔ 2/2018 (ኢዜአ):- በኢሉባቦር ዞን በሙዝ ልማት ላይ የተሰማሩ አርሶ አደሮችና ወጣቶች፣ ከምርቱ የሚያገኙት ገቢ እየጨመረ በመምጣቱ ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነታቸው እያደገ መሆኑን ገለጹ።
በዶረኒ ወረዳ የኤና ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት አርሶ አደር ጌታቸው ወርቅነህ፤ ከአራት ዓመት በፊት አነስተኛ መሬት ላይ ሙዝ ማልማት መጀመራቸውን ይናገራሉ።
በአሁኑ ወቅት የሙዝ ችግኝ እያበዙ መሆናቸውን የገለጹት አርሶ አደሩ፣ ልማቱን ወደ ግማሽ ሄክታር መሬት በማስፋት በሚያገኙት ገቢ ኑሯቸውን ማሻሻል መቻላቸውን ገልጸዋል።

ዘመናዊ የሙዝ አመራረት ዘዴዎችን በመጠቀም የምርት ጥራትና መጠናቸውን ማሳደግ በመቻላቸው ገቢያቸው በተሻለ ሁኔታ እያደገ መሆኑን ጠቁመው፤ ባለፈው ዓመት ከችግኝና ከምርት ሽያጭ እስከ 600 ሺህ ብር ገቢ ማግኘታቸውንና በዚህ ዓመትም የተሻለ ገቢ እንደሚጠብቁ አስረድተዋል።
የሙዝ ልማት ስራው ልጆቼን ለማስተማርና የተሻለ ሕይወት ለመምራት አግዞኛል ያሉት አርሶ አደር ጌታቸው፤ ወደፊት ልማቱን ይበልጥ በማስፋፋት ወደ ኢንቨስትመንት የመሸጋገር እቅድ እንዳላቸውም አጋርተዋል።

የአርሶ አደር ጌታቸውን ስኬታማ ተሞክሮ በመቅሰም በወረዳው የሚገኙ በርካታ ወጣቶች በፍራፍሬ ልማት ለመሰማራት ተነሳስተዋል።
የዚሁ ቀበሌ ነዋሪ የሆኑት ወጣት ወንድሙ ለገሰ እና ወጣት አዲሱ ያሲን ከሌሎች ጓደኞቻቸው ጋር በመደራጀት በአንድ ሄክታር መሬት ላይ የሙዝ ችግኝ መትከል መጀመራቸውን ገልጸዋል።
በተመሳሳይ ወጣት አዲሱ እምሩ እና ወጣት ምሬሳ ደረጄ በበኩላቸው፤ በሙዝ ልማት ላይ ጠንክረው በመስራት ተጠቃሚ ለመሆን መነሳታቸውን ጠቁመው፣ በተለይም የሙዝ ልማቱን ከሌሎች ጥምር የግብርና ስራዎች ጋር በማስተሳሰር ለማከናወን ማቀዳቸውን ተናግረዋል።

የዶረኒ ወረዳ ግብርናና መሬት ልማት አስተዳደር ጽሕፈት ቤት ኃላፊ ወይዘሮ ለሊሴ አመና እንደገለጹት፤ በወረዳው ከፍተኛ ትኩረት ከተሰጣቸው የግብርና ኢኒሼቲቮች መካከል የፍራፍሬ ልማት አንዱ ነው።
በአሁኑ ወቅት የፍራፍሬ ልማቱ በየቀበሌው በኩታ ገጠም አሰራር እየተከናወነ የሚገኝ ሲሆን፤ ከ1 ሺህ 600 ሄክታር በላይ መሬት በማኅበር በተደራጁ ወጣቶችና በአርሶ አደሮች እየለማ ይገኛል ብለዋል።
የአርሶ አደሩን ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተመዘገበ ያለውን ውጤት ይበልጥ ለማሳደግ በትኩረት እንደሚሰራም ኃላፊዋ አረጋግጠዋል።

የኢሉአባቦር ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ ዳኜ ፍቅሬ በበኩላቸው፤ በዞኑ በዚህ የክረምት ወቅት ከ29 ሺህ 100 ሄክታር በላይ መሬት በተለያዩ የፍራፍሬ ችግኞች የሚሸፈን ሲሆን፣ ከዚህ ውስጥ 4 ሺህ 300 ሄክታሩ በሙዝ ችግኝ የሚሸፈን መሆኑን አስታውቀዋል።
በዞኑ በአሁኑ ወቅት ሙዝን ጨምሮ አቮካዶ፣ አናናስ፣ ፓፓያና ሌሎች የፍራፍሬ ዓይነቶች በስፋት እየለሙ እንደሚገኙም ምክትል ኃላፊው ገልጸዋል።
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026
ሀዋሳ ፤ ግንቦት 28/2018 (ኢዜአ) ፦በይርጋለም የተቀናጀ የግብርና ኢንዱስትሪ ማቀነባበሪያ ፓርክ ከአምራች ኢንዲስትሪዎች ጋር በተፈጠረላቸው የገበያ ትስስር ...
Jun 6, 2026
ነገሌ ቦረና፤ ግንቦት 19/2018(ኢዜአ)፦ የነገሌ ቦረና ገዳ አውሮፕላን ማረፊያ አገልግሎት መጀመር የአካባቢውን ማህበራዊና ኢኮኖሚያዊ እንቅስቃሴ የበለጠ የሚያ...
May 28, 2026
ሀዋሳ፤ ግንቦት 11/2018 (ኢዜአ)፡- የሀዋሳ ከተማን ፈጣን እድገት የሚያሳልጡ የመሰረተ ልማት ግንባታዎች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የሲዳማ ክልል ርዕሰ መስተዳ...
May 20, 2026