የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ወደፊት እየገሰገሰች ነው - ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ

Jun 10, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦ ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈች ተስፋዎቿን እየጨበጠች ወደፊት እየገሰገሰች ነው ሲሉ የኢፌዴሪ ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትር ተመስገን ጥሩነህ ገለጹ፡፡

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ በወልድያ ከተማ የተገነቡ ልዩ ልዩ የልማት ፕሮጀክቶችን መርቀው ለአገልግሎት ከፍተዋል።


በምረቃው ወቅትም እንደገለጹት የተመረቁት የልማት ፕሮጀክቶች የሀገሪቱን ወደፊት የመገስገስ ጉዞ የሚያሳዩና የኢትዮጵያን ዕድገት ማንም ሊያስቆመው እንደማይችል ማረጋገጫዎች ናቸው።

ምክትል ጠቅላይ ሚኒስትሩ የወልድያ ከተማ ሕዝብ ጽንፈኝነትንና ከፋፋይነትን በመቃወም የሚታወቅ፣ ምርጫው ሰላምና ጠንካራ መንግሥት መሆኑን በየጊዜው ማሳየቱን ገልጸዋል።

መንግሥት ትግሉ ከተወሰኑ አካባቢ ሽፍቶች ጋር ሳይሆን መንገዳቸውን ክፍፍልና ድህነት ካደረጉ ቆሞ ቀር ኃይሎች ጋር መሆኑን ጠቅሰዋል።

ላለፉት 50 እና 60 ዓመታት ያረጀ አስተሳሰብ ይዘው የቆሙ አካላት የሀገሪቱን ፈጣን ጉዞ መገንዘብ እንዳልቻሉም አስረድተዋል።

በጫካ ያሉ አካላት የኮሪደር ልማትን፣ የሌማት ትሩፋትን፣ የገበታ ፕሮጀክቶችንና የስንዴ አብዮትን የመሰሉ በሀገሪቱ የመጡ ታላላቅ ለውጦችን ለማየት እንዳልታደሉ ገልጸዋል።

በከተሞች የሚካሄደው የኮሪደር ልማት የውበት ጉዳይ ብቻ ሳይሆን ከተሞችን የማዘመንና የሕዝብን የኑሮ ደረጃ ከፍ የማድረግ ዓላማ በማንገብ በመስፋፋት ላይ ነው ብለዋል።


የኢትዮጵያ ከተሞች ፉክክር ከምሥራቅ አፍሪካና ከዓለም ከተሞች ጋር መሆን እንዳለበት የገለጹ ሲሆን፤ አገልግሎትን ለማዘመንም መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት በመላ ሀገሪቱ እየተስፋፋ መሆኑን ጠቁመዋል።

በወልድያ ከተማ የተገነቡት የሕዝብ ቤተ መጻሕፍት፣ የዲጂታል ቤተ መጻሕፍትና የሳይንስ ካፌዎች ትውልዱን ከዕለት መረጃ ወደ ጥልቅ ዕውቀትና ምርምር የሚያሸጋግሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።


የገበያ ማዕከላትና የሱቆች ፕሮጀክቶች የንግድ እንቅስቃሴን በማሳለጥ ከፍተኛ ሚና እንዳላቸውና በሌማት ትሩፋት አማካኝነትም በምግብ ራስን የመቻል ጉዞው ተጠናክሮ መቀጠል እንዳለበት አሳስበዋል።

ኢትዮጵያ ዕዳዎቿን እያራገፈችና ተስፋዎቿን እየጨበጠች መጓዟን እንደምትቀጥል የገለጹት አቶ ተመስገን፣ ጠላት ቢሰበሰብ የሀገሪቱን ጉዞ ማደናቀፍ እንደማይችል አጽንኦት ሰጥተዋል።


የተጀመሩ የልማት ሥራዎችን ወደ ገጠር ጭምር በማስፋፋት የሀገሪቱን ብልጽግና እውን ለማድረግ መንግሥት፣ ባለሃብቱና ሕዝቡ በጋራ ሊሠሩ እንደሚገባ ጥሪ አቅርበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026