የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

መንግስት ጠንካራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሥርዓት ገንብቷል

Jun 14, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 5/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት አቅም የሚፈጥሩ ሙያተኞችና ቴክኖሎጂዎች ውጤታማ የሚሆኑበት ጠንካራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሥርዓትና ምቹ ምኅዳር መገንባቱን የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር) ገለጹ፡፡

የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ለተከታታይ ሶስት ቀናት የሚቆይ የመጀመሪያውን ዓለምአቀፍ የምርምር ጉባኤ እና የቴክኖሎጂ ውድድር ማካሄድ ጀምሯል።

በመድረኩ የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር)፣ ከተለያዩ ዓለም አቀፍ ሀገራት የመጡ ተመራማሪዎች፣ የቴክኖሎጂ ተወዳዳሪዎችና ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።


በመክፈቻው የሥራና ክህሎት ሚኒስትር ዴኤታ ተሻለ በሬቻ (ዶ/ር)፤ መንግስት ጠንካራ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና ሥርዓትን በመገንባት፣ ለሀገሪቱ ሁለንተናዊ ዕድገት አቅም የሚፈጥሩ ሙያተኞችና ቴክኖሎጂዎች ውጤታማ የሚሆኑበት ምቹ ምኅዳር ፈጥሯል ብለዋል።

ከሀገራዊ የልማት እድገት ጋር የተናበበ የቴክኒክና ሙያ ስልጠና እንዲጎለብት መንግስት የዘርፉን እድገት የሚያረጋግጡ ፖሊሲዎችና አሰራሮች ተግባራዊ ማድረጉን ጠቁመዋል።

በዘርፉ ብቁ ሙያተኛን በማፍራትና ቴክኖሎጂዎችን በማፍለቅ ለኢንዱስትሪላይዜሽን እድገት ምላሽ የሚሰጥ፣ አካታችና ጥራት ያለው የቴክኒክና ሙያ ሥርዓት መገንባት የሚያስችል ምኅዳር እየተፈጠረ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

በተለይም ብቁ፣ ቴክኖሎጂ የሚያፈልቁና በዓለም አቀፍ ደረጃ ተወዳዳሪ መሆን የሚችሉ ሰልጣኞችን በማፍራት በኩል አበረታች ለውጥ መመዝገቡን አክለዋል።

ለእነዚህ ስኬቶች ዋና ምክንያት ከሆኑት መካከል ገበያ መር ሥልጠና፣ የኢንዱስትሪ ተሳትፎ፣ አካታችነት፣ ዲጂታላይዜሽን እንዲሁም የፈጠራ እና የኢንተርፕረነርሺፕ ሥነ-ምህዳር ማጎልበት በመቻሉ መሆኑን አስረድተዋል።

በቀጣይም የኢንዱስትሪላይዜሽን እድገትን ለማፋጠንና ቀጣይነት ያለው የኢኮኖሚ እድገት ለማስመዝገብ ጠንካራ የቴክኒክና ሙያ ሥርዓትን ማጠናከርና ከዓለም አቀፍ ሀገራት ጋር በጋራ መስራት እጅግ አስፈላጊ መሆኑን ጠቅሰዋል።

ለዚህ ደግሞ የቴክኖሎጂ ምርምር ሥራዎች ወሳኝ በመሆናቸው፣ ዛሬ የተጀመረው ዓለም አቀፍ ጉባኤና የቴክኖሎጂ ውድድር የእውቀትና የቴክኖሎጂ ሽግግር እንዲጎለብት ትልቅ አቅም እንደሚፈጥር ገልጸዋል።


የኢፌዲሪ ቴክኒክና ሙያ ስልጠና ኢንስቲትዩት ዋና ዳይሬክተር ብሩክ ከድር (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ በተዘጋጀው የሦስት ቀናት ጉባኤ ዘርፉ ላይ ያተኮሩ የምርምር ጽሑፎች እንደሚቀርቡና የተመረጡ የቴክኖሎጂ ሥራዎች ለውድድር እንደሚበቁ አብራርተዋል።

በዚህ ታላቅ ሁነት ላይ ከ16 በላይ ሀገራት የተውጣጡ ተመራማሪዎችና ባለድርሻ አካላት እየተሳተፉ መሆናቸውን አስታውቀዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026