🔇Unmute
አዲስ አበባ፣ ሰኔ 5 / 2018 (ኢዜአ)፦ ከቅርብ ዓመታት ወዲህ በአዲስ አበባ ከተማ ከታየው አስደማሚ የከተሜነት ትራንስፎርሜሽን ጎን ለጎን የሕብረተሰብ ተጠቃሚነትን ማዕከል ያደረጉ ዘመን ተሻጋሪ ሰው ተኮር ስራዎች ተሰርቷል፤ እየተሰሩም ይገኛሉ፡፡
ከነዚህ ውስጥ የህዝቡ የዘመናት ጥያቄ የነበረውን የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለት ስር-ነቀል የሆነ ለውጥ ለማምጣትም መጠነ ሰፊ የሆነ የመሰረተ-ልማት እና የሰው ኃይል ልማት እየተሰራ ይገኛል፡፡
ዕድገቷን እና ስሉጥ ከተማነቷን (Smart-city) የሚመጥን አገልግሎት ለማቅረብ ቴክኖሎጂን ተግባር ላይ የማዋል ሂደት አጠናክራ ይዛለች፡፡ ይኸውም የመሶብ አንድ ማዕከል ዲጂታል አገልግሎት ቀዳሚው ተጠቃሽ ነው፡፡

አዲስ መሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት፣ በከተማዋ ሁሉም ክፍለ ከተሞች ተደራሽ በማድረግ የሕብረተሰቡን የአገልግሎት አሰጣጥ ለማዘመን ቀን ከሌሊት እየተሰራ ይገኛል፤ የላቀ ውጤትም ተመዝግቦበታል፡፡
እስካሁን በማዕከል እና በዘጠኝ ክፍለ-ከተሞች እንዲሁም በተንቀሳቃሽ አውቶቡስ የተደራጀ፣ ጥብቅ ክትትልና ድጋፍ የሚደረግባቸው፣ የበቁ የሰው ኃይል የተሟላላቸው ማዕከሎች አገልግሎት እየሰጡ ይገኛሉ፡፡
በቴክኖሎጂ በታገዘ በተደረገ ዳሰሳ እንደሚያሳየው ተገልጋዩ ከ99 በመቶ በላይ እርካታ ያመላክታል፡፡ ቀሪ ሁለት ክፍለ ከተሞችም ግንባታቸው ተጠናቅቆ በጥቂት ቀናት አገልግሎት ይጀምራሉ፡፡

የአገልግሎት አሰጣጥ ጉድለትን ታሪክ ለማድረግ በቁርጠኝነት ተተግብሮ፣ የሕብተሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ለማላቅ እንደሚሰራ የከተማ አስተዳደሩ ከንቲባ ጽ/ቤት መረጃ ያመለክታል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026