የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ብልጽግና ፓርቲ ህዝብ የሰጠውን ኃላፊነት በመወጣት የተጀመሩ የልማት ስራዎችን ማስቀጠል ይጠበቅበታል

Jun 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሰኔ 15/2018 (ኢዜአ)፦ ብልጽግና ፓርቲ ሕዝብ የሰጠውን አደራና ኃላፊነት በመወጣት፣ የተጀመሩ የልማትና የመልካም አስተዳደር ሥራዎችን አጠናክሮ ማስቀጠል እንዳለበት የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች ገለጹ።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ባስታወቀው መሠረት ብልጽግና ፓርቲ የ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫዎችን በማግኘት አሸንፏል።

በዚሁ ጉዳይ ላይ ኢዜአ ያነጋገራቸው የአሶሳ ከተማ ነዋሪዎች፤ አሸናፊው ብልጽግና ፓርቲ ተጨማሪ የህዝብ አደራን በመቀበል ለቀጣይ አምስት ዓመታት መሠረታዊ የልማት ስራዎችን ለማከናወን የሚያስችለውን ዕድል አግኝቷል።

ከነዋሪዎቹ መካከል አቶ አልሃጂ ሀሊፋ እንደተናገሩት፤ የምርጫው ውጤት ብልጽግና ፓርቲ እያከናወናቸው የሚገኙ ትላልቅ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ የተሻለች ሀገር ለመገንባት በሚደረገው ሂደት አዎንታዊ ሚና ይኖረዋል።

ፓርቲው የህዝቡን ይሁንታ ያገኘ በመሆኑ ከህዝቡ የሚነሱ የልማት፣ የመልካም አስተዳደርና ሰላም የማስከበር ጥያቄዎችን ለመመለስ ከመቼውም ጊዜ በላይ ዝግጁ መሆን እንዳለበትም ገልጸዋል።

ሌላው የከተማዋ ነዋሪ አቶ ጉዴታ ነጋሳ በበኩላቸው፤ 7ኛው ጠቅላላ ምርጫ በሁሉም መስክ ስኬታማ መሆኑን ገልጸው፤ በተለይም በህዝብ ተወካዮች እና በክልል ምክርቤቶች ተፎካካሪ ፖለቲካ ፓርቲዎችም ከዚህ በፊት ከነበረው የተሻለ መቀመጫ ማግኘታቸው የፖለቲካ ምህዳሩ እየሰፋ መምጣቱን ያሳያል ብለዋል።

አሸናፊው ብልጽግና ፓርቲም ያገኘውን ዕድል በመጠቀም በሁሉም አካባቢዎች አስተማማኝ ሰላም እንዲሰፍን እና የልማት ስራዎች ተጠናክረው እንዲቀጥሉ ትልቅ የቤት ስራ እንደሚጠብቀው ተናግረዋል።

የምርጫው ውጤት የኢትዮጵያን አሸናፊነት ያረጋገጠ እና የህዝብ ድምጽ ምን ያክል ዋጋ እንዳለው ያስመሰከረበት ነው ያሉት ደግሞ የከተማዋ ነዋሪ አቶ አደም ሳለህ ናቸው።

የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ የምርጫ ሂደቱን ነፃ እና ገለልተኛ ሆኖ ያከናወነበት ሁኔታ የሚደነቅ መሆኑን በመጥቀስ።

በ7ኛው ጠቅላላ ምርጫ ለሕዝብ ተወካዮች እና ለክልል ምክር ቤቶች ብልጽግና ፓርቲ አብላጫ የምክር ቤት መቀመጫ በማግኘት ማሸነፉን የኢትዮጵያ ብሔራዊ ምርጫ ቦርድ ትናንት ይፋ ማድረጉ የሚታወስ ነው።

የምርጫው ውጤት ይፋ መደረጉን ተከትሎም ብልጽግና ፓርቲ ለመላው የኢትዮጵያ ህዝብ ምስጋና ያቀረበ ሲሆን፤ ፓርቲው በቅድመ ምርጫ ለህዝብ የገባውን ቃል ሳይሸራረፍ በመተግበር ሕዝብን በቅንነትና በታማኝነት እንደሚያገለግልም አረጋግጧል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026