የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በአቅራቢያችን መኖሩ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንድናገኝ አስችሎናል - ሸማቾች

Jun 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ ፤ ሰኔ 20/2018 (ኢዜአ)፦የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በአቅራቢያቸው መኖሩ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ ማግኘት እንዳስቻላቸው ሸማቾች ገለጹ።

መንግስት አላስፈላጊ የዋጋ ንረትን ለመከላከልና ገበያውን ለማረጋጋት የተለያዩ የግብይት አማራጮችን በመዘርጋት ሸማቾች መሰረታዊ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ የተለያዩ ተግበራት ማከናወኑ ይታወቃል።

የቅዳሜና እሁድ ገበያዎች በተለያዩ አካባቢዎች ላይ ሕብረተሰቡ ምርቶችን በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ በማድረግና ገበያን በማረጋጋት ረገድ ትልቅ አስተዋጽኦ እያበረከቱ መሆኑ ይታወቃል።

ኢዜአ በተለያዩ በአዲስ አበባ በተለያዩ አካባቢዎች የቅዳሜና እሁድ ገበያ ስፍራዎች ላይ በመገኘት ቅኝት አድርጓል።


ሐሳባቸውን ካጋሩን አስተያየት ሰጪዎች መካከል ወይዘሮ ሰናይት ብዙአየው እንዳሉት፤ የቅዳሜና እሁድ ገበያ የተለያዩ ጥራት ያላቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ የሚያገኙበት ስፍራ ነው።

ገበያው የኑሮ ውድነትን ለመቋቋም አቅም ከመፍጠር ባሻገር፣ የተለያዩ ምርቶችን በቀጥታ ማግኘት የሚያስችል በመሆኑ ተመራጭ ነው ብለዋል።

በገበያው በርካታ ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ መቅረባቸው ለሕብረተሰቡ እፎይታ መስጠቱን ገልጸው ገበያው በአቅራቢያቸው መሆኑ ጊዜያቸውን በአግባቡ እንዲጠቀሙ እንዳስቻላቸው ገልጸዋል፡፡


አቶ ገዳሙ ይበልጣል እና ወይዘሮ አበበች ጎሽም በበኩላቸው፤ ገበያው ከመደበኛው ገበያ ምርቶችን ከፍተኛ ቅናሽ ያለውና የሕብረተሰቡን ገቢ ታሳቢ ያደረገ በመሆኑ ለእኛ ተመራጭ ነው ብለዋል።


በአቅራቢያቸው መኖሩ የግብይት ሥርዓቱን ቀልጣፋ እና ምቹ እንዳደረገላቸው ጠቅሰው የዋጋ ንረትን ለማረጋጋት ትልቅ አስተዋፅኦ እንዳለው ተናግረዋል።

በቅዳሜ እና እሁድ ገበያ ላይ በመሳተፍ የግብርና እና የኢንዱስትሪ ምርቶችን የሚያቀርቡ ነጋዴዎች በበኩላቸው፤ ወደ ገበያው ለሚመጡ ሸማቾች ጥራት ያላቸውን ምርቶች በተመጣጣኝ ዋጋ እያቀረቡ መሆኑን ገልጸዋል።


ከአስተያየት ሰጪዎቹ መካከል አቶ ፈቃዱ አሜጋ እና አቶ ተመቸው መቻል በሰጡት አስተያየት፤ ሸማቹ የተሻለ ጥራት ያለው ምርት በተመጣጣኝ ዋጋ እንዲያገኙ ማድረግ መቸላቻውን ጠቅሰዋል፡፡

በተጨማሪም መንግሥት የንግድ ቦታዎችን በነፃ ከማመቻቸቱ ባሻገር፣ ምርቶችን ከአቅራቢዎች በቀላሉ አግኝተው ለኅብረተሰቡ እንዲያቀርቡ ዕድል መፍጠሩንም ገልጸዋል፡፡

ይህም ምርቶችን በበቂ ሁኔታና በተመጣጣኝ ዋጋ ለሸማቹ ለማቅረብ ትልቅ ምቹ ሁኔታ እንደፈጠረላቸው ገልጸዋል።


የአዲስ አበባ ንግድ ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ሀቢባ ሲራጅ በሰጡት አስተያየትም፤ መንግሰት የኑሮ ውድነትን ጫና ለመቀነስና የህብረተሰቡን ፍላጎት ለማሟላት በርካታ ስራዎችን እየሰራ ይገኛል፡፡

አስተዳደሩ በከተማዋ ትላልቅ የገበያ ማዕከላትን ከመገንባት ጎን ለጎን የቅዳሜና እሁድ ገበያዎችን የማስፋት ስራ በመስራት በርካቶችን ተጠቃሚ ማድረጉን ተናግረዋል፡፡

በመካከለኛና ዝቅተኛ ደረጃ ላይ ያሉ ዜጎችን የኑሮ ውድነት ጫና ለማቃለል ከመደበኛው ገበያ የ20 በመቶ ቅናሽ ተደርጎ ምርቶች እየቀረቡ ሲሆን፣ ምርቶች በቀጥታ ከአምራቹ ለሸማቹ እንዲደርሱ እየተደረገ ይገኛል ብለዋል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026