🔇Unmute
አዲስ አበባ፤ሐምሌ 2/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ ለኢንቨስትመንት፣ ለንግድና ለቀጣናዊ ደህንነት መረጋገጥ ቁልፍ ስትራቴጂያዊ ጠቀሜታ ያላት ሀገር መሆኗን የተለያዩ ሀገራት አምባሳደሮች ገለጹ።
ከኢትዮጵያ ጋር ያላቸውን የሁለትዮሽ አጋርነት ለማጠናከር ፍላጎት እንዳላቸው አምባሳደሮቹ አንስተዋል።
ከኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ጋር ቆይታ ያደረጉ አምባሳደሮች በሰጡት አስተያየት፤ ኢትዮጵያ ኢኮኖሚዋን በማሳደግ ረገድ የምታደርገው ጥረት ከጠንካራ የትራንስፖርት ትስስር ጋር ተዳምሮ ቀጣናዊ የማዕከልነት ደረጃዋን አጠናክሮታል ብለዋል።
በኢትዮጵያ የሮማኒያ አምባሳደር ጁሊያ ፓታኪ እንደገለጹት፤ ኢትዮጵያ በቀጣናው ኢኮኖሚያዊ ውህደት እንዲሳለጥ እንዲሁም ሰላምና ደህንነት እንዲጠበቅ እየተጫወተች ያለው ሚና የሚደነቅ ነው።
ኢትዮጵያ በአፍሪካ ፈጣን ዕድገት እያስመዘገቡ ካሉ ሀገራት ግንባር ቀደም መሆኗን የጠቀሱት አምባሳደሯ፤ ነፃ ንግድ እና የገበያ ትስስር በአህጉቱ ያለውን የኢኮኖሚ ልማት ለማፋጠን አስፈላጊ መሆናቸውን አመልክተዋል።
አዲስ አበባ የአፍሪካ ህብረት መቀመጫ መሆኗና ታሪካዊ ሚናዋ ኢትዮጵያን ለዲፕሎማሲ እና የአፍሪካን ተግዳሮቶች ለመፍታት በሚደረጉ የጋራ ጥረቶች ተመራጭ ሀገር እንዳደረጋት አብራርተዋል።

በኢትዮጵያ የኦማን ሚሲዮን መሪ አፍካር አል ፋርሲ በበኩላቸው፤ ኢትዮጵያ ባላት ሰፊ መልክዓ ምድራዊ አቀማመጥና በማደግ ላይ ባለው ኢኮኖሚዋ ሳቢያ በቀጣናው ወሳኝ ሀገር ናት ብለዋል።
ቀጣናውን የማስተሳሰር አህጉራዊ ሚናዋ እያደገ ነው ያሉት ሚሲዮን መሪው፤ በአፍሪካ ግዙፉ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ለቀጣናዊ እና ለአህጉራዊ ውህደት ትልቅ አስተዋፅኦ አለው ሲሉ ገልጸዋል።
በንግድ እና በኢንቨስትመንት ዙሪያ የኢትዮጵያ እና የኦማን የሁለትዮሽ ግንኙነት እየጎለበተ መምጣቱን ጠቁመው፤ ኦማን የብረት ምርቶችን እና የፕላስቲክ ፓሌቶችን ወደ ኢትዮጵያ ስትልክ፣ ኢትዮጵያ ደግሞ ቡና፣ ሰሊጥ እና ሌሎች የግብርና ምርቶችን ወደ ኦማን እንደምትልክ አስረድተዋል።
በሀገራቱ መካከል ያለውን የንግድ ልውውጥ ይበልጥ ማስፋት የሚቻልበት ዕድል መኖሩን ጠቅሰው፥ ኦማን በተለያዩ መስኮች ከኢትዮጵያ ጋር ያላትን የሁለትዮሽ ግንኙነት ለማሳደግ ፍላጎት እንዳላት ጠቁመዋል።
በኢትዮጵያ በሪል ስቴት እና መሰረተ ልማት ፕሮጀክቶች፣ በአምራች፣ በኮንስትራክሽንና በግብርና ዘርፎች የኦማን ባለሀብቶች ሊሰማሩባቸው የሚችሉባቸው ሰፊ የኢንቨስትመንት አማራጮች መኖራቸውን ጠቅሰዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026