🔇Unmute
ገንዳውኃ፤ ሐምሌ 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የተገኘው ሰላም የግብርና ስራቸውን በተረጋጋና በተደራጀ መልኩ ማከናወን እንዳስቻላቸው አርሶ አደሮች ተናገሩ።
አርሶ አደር ሱሌማን ዳውድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአካባቢያችን ሰላም ለማስጠበቅ ባደረግናቸው ጥረቶች የእርሻ ስራችን በተገቢው መንገድ ለማከናወን አስችሎናል።
በአሁኑ ወቅትም በ10 ሄክታር መሬታቸውን በሰሊጥ፣ በአኩሪ አተርና ሌሎች ሰብሎች ለመሸፈን የዘር ስራ መጀመራቸውን ነው የገለጹት።
አርሶ አደር ደጀኔ አሰፋ በበኩላቸው፣ ዞኑ ለግብርና ልማት ያለው ፀጋ ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በስፋት ለማምረት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።
በዘንድሮው ክረምትም ባለኝ 20 ሔክታር መሬት ላይ ጥጥ፣ ሰሊጥ፣ አኩሪ አተርና ሌሎች ሰብሎችን በመዝራት እስከ 200 ኩንታል ምርት ለማግኘት እየሰራሁ ነው ብለዋል።
በአካባቢው የተፈጠረው ሰላም አርሶ አደሩ፣ ባለሃብቱና የጉልበት ሰራተኛው ተረጋግቶ እንዲሰራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የገለጹት ደግሞ በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ቃሲም እንድሪስ ናቸው።
ያላቸውን 65 ሄክታር መሬት በዘመናዊ መንገድ በማልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።
የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ እንደገለጹት፤ ማሕበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ ከአመራሩ እና ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል።
በዚህም አስተማማኝ ሰላም እየተፈጠረ በመምጣቱ በዘመናዊ ትራክተሮችና ሜካናይዜሽን ታግዞ የግብርና ስራን ለማቀላጠፍ እንተቻለ ነው የተናገሩት።
በተገኘው ሰላም ለአርሶ አደሩና ባለሃብቱ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና የምርት ማሳደጊያ ግብዓትን በወቅቱ ለማቅረብም እንደተቻለ ነው ያመለከቱት።
በዘንድሮው የመኸር እርሻ529 ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ከ450 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በዘር ተሽፍኗል ብለዋል።
የዞኑ ህብረተሰብም ሰላም የሁሉም መሰረት መሆኑን በመገንዘብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያረጋገጠውን ሰላም አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026