የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በዞኑ የተገኘው ሰላም የግብርና ስራችንን በተረጋጋና በተደራጀ መልኩ ለማከናወን አስችሎናል - አርሶ አደሮች

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ገንዳውኃ፤ ሐምሌ 4/2018(ኢዜአ)፦ በአማራ ክልል ምዕራብ ጎንደር ዞን የተገኘው ሰላም የግብርና ስራቸውን በተረጋጋና በተደራጀ መልኩ ማከናወን እንዳስቻላቸው አርሶ አደሮች ተናገሩ።

አርሶ አደር ሱሌማን ዳውድ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ የአካባቢያችን ሰላም ለማስጠበቅ ባደረግናቸው ጥረቶች የእርሻ ስራችን በተገቢው መንገድ ለማከናወን አስችሎናል።

በአሁኑ ወቅትም በ10 ሄክታር መሬታቸውን በሰሊጥ፣ በአኩሪ አተርና ሌሎች ሰብሎች ለመሸፈን የዘር ስራ መጀመራቸውን ነው የገለጹት።

አርሶ አደር ደጀኔ አሰፋ በበኩላቸው፣ ዞኑ ለግብርና ልማት ያለው ፀጋ ለወጭ ንግድ የሚሆኑ ምርቶችን በስፋት ለማምረት እንዳስቻላቸው ገልጸዋል።

በዘንድሮው ክረምትም ባለኝ 20 ሔክታር መሬት ላይ ጥጥ፣ ሰሊጥ፣ አኩሪ አተርና ሌሎች ሰብሎችን በመዝራት እስከ 200 ኩንታል ምርት ለማግኘት እየሰራሁ ነው ብለዋል።

በአካባቢው የተፈጠረው ሰላም አርሶ አደሩ፣ ባለሃብቱና የጉልበት ሰራተኛው ተረጋግቶ እንዲሰራ ምቹ ሁኔታ መፍጠሩን የገለጹት ደግሞ በእርሻ ኢንቨስትመንት የተሰማሩት አቶ ቃሲም እንድሪስ ናቸው።

ያላቸውን 65 ሄክታር መሬት በዘመናዊ መንገድ በማልማት ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ እየሰሩ መሆኑን ተናግረዋል።

የምዕራብ ጎንደር ዞን አስተዳዳሪና የግብርና መምሪያ ኃላፊ አንዳርጌ ጌጡ እንደገለጹት፤ ማሕበረሰቡ የአካባቢውን ሰላም ለማረጋገጥ ከአመራሩ እና ከጸጥታ ኃይሉ ጋር በቅንጅት እየሰራ ይገኛል።

በዚህም አስተማማኝ ሰላም እየተፈጠረ በመምጣቱ በዘመናዊ ትራክተሮችና ሜካናይዜሽን ታግዞ የግብርና ስራን ለማቀላጠፍ እንተቻለ ነው የተናገሩት።

በተገኘው ሰላም ለአርሶ አደሩና ባለሃብቱ ዘመናዊ የቴክኖሎጂ ውጤቶችና የምርት ማሳደጊያ ግብዓትን በወቅቱ ለማቅረብም እንደተቻለ ነው ያመለከቱት።

በዘንድሮው የመኸር እርሻ529 ሺህ ሄክታር መሬት ለማልማት ታቅዶ ወደ ስራ የተገባ ሲሆን በአሁኑ ወቅትም ከ450 ሺህ ሄክታር በላይ ማሳ በዘር ተሽፍኗል ብለዋል።

የዞኑ ህብረተሰብም ሰላም የሁሉም መሰረት መሆኑን በመገንዘብ ከጸጥታ አካላት ጎን በመሰለፍ ያረጋገጠውን ሰላም አጠናክሮ መቀጠል እንደሚገባው አስገንዝበዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026