የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞሪሺየስ የጀመረው አዲስ ቀጥታ በረራ ለንግድ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት አዳዲስ ዕድሎችን ይፈጥራል

Jul 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 4/2018(ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞሪሺየስ የጀመረው አዲስ ቀጥታ በረራ ለንግድ፣ ለቱሪዝምና ለኢንቨስትመንት አዳዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥር የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ ገለጹ፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞሪሺየስ ዋና ከተማ ፖርት ሉዊስ የቀጥታ በረራ መጀመሩን ይፋ አድርጓል፡፡

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ወደ ሞሪሺየስ የጀመረው አዲስ ቀጥታ በረራ የአፍሪካን ተደራሽነት በማስፋት የትስስር ጥረቱን የሚያጠናክር ስኬታማ ምዕራፍ ነው ተብሏል፡፡

የበረራው ማስጀመሪያ የመርሐግብር ላይ የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ፣ የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ስራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው፣ በኢትዮጵያ የሞሪሺየስ ሪፐብሊክ አምባሳደር ኢንድራርጂት ባምቦዋ እና ሌሎች ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች ተገኝተዋል።

በመርሐግብሩ ንግግር ያደረጉት የውጭ ጉዳይ ሚኒስትር ዴኤታ አምባሳደር ሃደራ አበራ እንዳሉት፣ አዲሱ የበረራ አገልግሎት የሁለቱ ሀገራት የአፍሪካ ውህደትን ለማጠናከር ያላቸውን ቁርጠኝነት ያሳያል።

ይህ ድልድይ ለቀጠናዊ ትስስር፣ ለንግድ፣ ለቱሪዝም፣ ለኢንቨስትመንትና ለባሕል ልውውጥ አዳዲስ ዕድሎችን እንደሚፈጥር ገልጸዋል።

በሞሪሺየስ እና በአዲስ አበባ በኩል ወደ ቀሪው ዓለም የሚደረገውን ጉዞ በማቀላጠፍ ዲፕሎማሲያዊ ግንኙነቱን እንደሚያጠናክሩ ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድ ግሩፕ ዋና ሥራ አስፈጻሚ መስፍን ጣሰው በበኩላቸው፣ አዲሱ መስመር አየር መንገዱ በአፍሪካ ያለውን ትስስር ለማሳደግ ያለውን ስትራቴጂያዊ እቅድ ያሳያል ብለዋል።

ሞሪሺየስ የአየር መንገዱ 41ኛዋ የአፍሪካ መዳረሻ መሆኗን የጠቆሙት ዋና ስራ አስፈጻሚው፣ ይህ በረራ የአፍሪካ አህጉራዊ ነፃ የንግድ ቀጠና (AfCFTA) ዓላማዎችን በመደገፍ የኢኮኖሚ ትብብርን እንደሚያሻሽል አስረድተዋል።

በኢትዮጵያ የሞሪሺየስ አምባሳደር ኢንደራርጂት ባምቡዋ፣ ይህ የበረራ መጀመር በሁለትዮሽ ግንኙነት ውስጥ የአዲስ ምዕራፍ መጀመሪያ መሆኑን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ አየር መንገድን የአፍሪካ ልቀት፣ ጽናትና ፈጠራ ምልክት ሲሉ ያደነቁ ሲሆን፣ አዲሱ መስመር በአፍሪካ እና በሕንድ ውቅያኖስ ቀጠና መካከል ያለውን ትስስር በእጅጉ እንደሚያሳድግም እምነታቸውን ገልጸዋል።

ይህ አዲስ የበረራ አገልግሎት የኢትዮጵያ አየር መንገድ አፍሪካን ከዓለም ጋር የሚያገናኝበትን መረብ ይበልጥ ያጠናክራል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026