የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ኢትዮጵያ የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ አገራት ድርጅት (አካፓድ) ሊቀመንበር ሆና ተመረጠች

Jul 19, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ሐምሌ 10/2018 (ኢዜአ)፦ኢትዮጵያ የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓሲፊክ አገራት ድርጅት (አካፓድ) ሊቀመንበር ሆና ተመርጣለች።

121ኛው የአካፓድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ ሐምሌ 8-9 ቀን 2018 ዓ.ም. ቤልጅየም መዲና ብራስልስ ተካሂዷል።

በጉባኤው ላይ በገንዘብ ሚኒስትር ዲኤታ ሰመሪታ ሰዋሰው የተመራ እና የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር የስራ ኃላፊዎችን ያካተተ የልኡካን ቡድን ኢትዮጵያን በመወከል ተሳትፏል።

የሚኒስትሮቹ ስብሰባ የትኩረት አጀንዳዎች የማላቦ ዲክላሬሽን አተገባበር ሂደትን መገምገም፣ የድርጅቱን የፋይናንስ አቅም በዘላቂነት ለመገንባት ስለሚወሰዱ እርምጃዎች መምከር ላይ ያተኮረ ነው።


እንዲሁም የድርጅቱ ማሻሻያ ሂደት ያለበትን ደረጃ መገምገም፣ የሳሞአ ስምምነትን የትግበራ ሂደት መገምገም እንዲሁም ሌሎች የድርጅቱንና የአባል ሀገራትን ጥቅም ስለሚያስጠብቁ ጉዳዮች ዙሪያ ውይይት ተደርጓል።

ኢትዮጵያ አቋሟን የሚያንጸባርቁ እና ድርጅቱን በፕሬዚዳንትነት በምትመራበት ወቅት የምትከተላቸውን የትኩረት አቅጣጫዎች የሚያመለክቱ ንግግሮች አቅርባለች።

በጉባኤው ማጠናቀቂያም ኢትዮጵያ ከኦገስት 1 ቀን 2026 እስከ ጃንዋሪ 31 ቀን 2027 የአፍሪካ፣ ካሪቢያንና ፓስፊክ አገራት ድርጅት የሚኒስትሮች ምክር ቤት ፕሬዚዳንት ሆና ተመርጣለች።

ኢትዮጵያ በቀጣይ ስድስት ወራት የጉባኤው ሰብሳቢነቷ ወቅት ቅድሚያ የምትሰጣቸውን የትኩረት ጉዳዮች አስተዋውቃለች።

እነዚህም ከወቅቱ ጂኦፖለቲካዊ እውነታ አኳያ የድርጅቱን ጽ/ቤትና የአባል አገራትን የፖሊሲ ነጻነት ማረጋገጥ፣ በራስ አቅም ሊከናወኑ ስለሚችሉ የልማት ስራዎችና የአገር ውስጥ ሃብት ማሰባሰብ የኢትዮጵያን ተሞክሮ በማጋራት በምሳሌነት መምራት፣ በተቋሙ ውስጥ ግልጽነትና ተጠያቂነት እንዲጠናከር በማድረግ የመልካም አስተዳደር ችግር እንዲወገድ መስራት፣ የድርጅቱ የፋይናንስ እጥረት በዘላቂነት እንዲፈታ የተጀመረው የሀብት ማሰባሰብ ጥረት ተጠናክሮ እንዲቀጥል ማድረግ እና የአውሮፓ ህብረት እና የአካፓድ ግንኙነት መሠረት የሆነው የሳሞአ ስምምነት አፈጻጸም በተሻለ መልኩ እንዲጓዝ መስራት ዋና ዋናዎቹ ናቸው።

ኢትዮጵያ ድርጅቱ ከተመሰረተ እ.ኤ.አ. 1975 ጀምሮ ሁለት ጊዜ (እ.ኤ.አ. ከነሀሴ 1 ቀን 1986 እስከ ጥር 31 ቀን 1987 እና ከየካቲት 1 ቀን 2017 ዓ.ም. እስከ ሀምሌ 31 ቀን 2017 ) ተቋሙን በሰብሳቢነት ማገልገሏን የውጭ ጉዳይ ሚኒስቴር ገልጿል።

በአሁኑ ወቅት ኢትዮጵያ የአካፓድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ሰብሳቢ ሆና መመረጧ፣ በዓለም አቀፍ መድረክ ያላትን የዲፕሎማሲ ተፅዕኖ ፈጣሪነት በድጋሚ የሚያረጋግጥ ታላቅ ስኬት መሆኑም ተገልጿል።

ይህ ታሪካዊ ኃላፊነት ኢትዮጵያ በደቡብ-ደቡብ ሁለንተናዊ ትብብር ላይ ያላትን ተሳትፎ ይበልጥ ከማጠናከሩ ባሻገር፣ ከአባል አገራቱና ከአውሮፓ ህብረት ጋር የሚደረጉ ትብብሮችን በበላይነት ለመምራት፣ ብሄራዊ ጥቅሟን ለማስከበር እና መልካም ገፅታዋን ለመገንባት የዲፕሎማሲ ዕድሎችን ይከፍታል።

ጉባኤውም ለኖቬምበር 2026 ዓ.ም. የታቀደው የ122ኛው የአካፓድ የሚኒስትሮች ምክር ቤት ስብሰባ በኢትዮጵያ አስተናጋጅነት አዲስ አበባ እንዲካሄድ በድርጅቱ አባል ሀገራት ተወስኖ ተጠናቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 19, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026