የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታ ለሚያጎለብቱ ተግባራት ትኩረት ተሰጥቷል

Jul 21, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅግጅጋ፤ ሐምሌ 13/2018(ኢዜአ)፦በሶማሌ ክልል የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን የሚያጎለብቱ ተግባራት በትኩረት እየተከናወኑ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ አስታወቁ።

የሶማሌ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ሙስጠፌ መሀመድ የክልሉን ኢኖቬሽን ማዕከል መርቀው ለአገልግሎት ክፍት አድርገዋል።


ርዕሰ መስተዳድሩ በወቅቱ እንደገለጹት፤ በክልሉ የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታና የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማጎልበት አገልግሎት አሰጣጡን ለማዘመንና የዲጂታል ኢኮኖሚን ለማሳለጥ ትኩረት ተሰጥቷል።

በዚህም የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን ጠቁመው የክልሉ የኢኖቬሽን ማዕከልም በቴክኖሎጂ ብቁ የሆኑ ዜጎችን ለማፍራት እና በዘርፉ አቅማቸውን ለማጠናከር ዕድል የሚፈጥር መሆኑን ተናግረዋል።

መንግሥት ለቴክኖሎጂና ኢኖቬሽን ልማት የሰጠው ትኩረት አበረታች ለውጦች እያስመዘገበ መሆኑን ጠቁመው ይህንኑ ለማስፋት እየተሠራ ነው ሲሉ አክለዋል። በቀጣይም ማዕከሉን የማስፋት፣ በግብአትና፣ በሙያተኞች የማጠናከር ስራ በትኩረት እንደሚከናወን አመላክተዋል።


የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ሃላፊ መሀመድ አሊ በበኩላቸው፤ ማዕከሉ የወጣቶችን የፈጠራ ችሎታና የቴክኖሎጂ አጠቃቀም አቅም የሚገነባና ክህሎታቸውን የሚያጎለብት መሆኑን ተናግረዋል።

ማእከሉ የ2030 የዲጂታል እቅድ ስትራቴጂን ለማሳካት ከፍተኛ አስተዋጽኦ የሚያበረክት መሆኑን ጠቁመው ይህንኑ ታሳቢ በማድረግ የተቋቋመ መሆኑን ተናግረዋል።


ማዕከሉ በድረገጽ ልማት፣ አርቲፊሻል ኢንተለጀንስ፣ በመረጃ ትንተና፣ ሳይበር ሴኩሪቲ፣ ዲጂታል ዲዛይን አገልግሎት በመሳሰሉት ስልጠና የሚሰጥበት መሆኑን ተናግረዋል።

ማዕከሉ በተጨማሪም አነስተኛ ንግዶችን የማልማትና የምርምር አገልግሎት የሚሰጥ መሆኑን ተናግረዋል።

በስነ ስርአቱ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ሃላፊዎች፣ ወጣቶች፣ የፈጠራ ባለሙያዎች፣ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች እና ባለድርሻ አካላት ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026