የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በራስ አቅም ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እየተገነባ ነው

Jul 22, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሐዋሳ፤ ሃምሌ 15/2018 (ኢዜአ)፡- በሲዳማ ክልል የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በራስ አቅም የተቀናጀና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እየተገነባ መሆኑን የክልሉ አደጋ ስጋት ስራ አመራርና የድጋፍ ማስተባበሪያ ኮሚሽን አስታወቀ፡፡

የሲዳማ ክልል አደጋ ስጋት ስራ አመራርና የድጋፍ ማስተባበሪያ ኮሚሽነር ሃይሉ ሃሰና፤ በክልሉ ለአደጋ ዝግጁ ከመሆንና ፈጣን ምላሽ ከመስጠት አንፃር እየተደረገ ያለውን ጥረት በተመለከተ ከኢዜአ ጋር ቆይታ አድርገዋል።


በማብራሪያቸውም በክልሉ ለአደጋ ጊዜ ዝግጁነትን ለማጠናከር ከሜቲዎሮሎጂ ኤጄንሲ፣ ከፌዴራል አደጋ ስጋት አመራር ኮሚሽን እና ሌሎችም የሚመለከታቸው አካላት ጋር ጠንካራ ትብብር በመፍጠር እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በመሆኑም የምርት አቅምን በማሳደግ ለአደጋዎች ፈጣንና የተሟላ ምላሽ ለመስጠት የሚያስችል ዝግጅት ከማድረግ ባለፈ የቅድመ ማስጠንቀቂያና የግንዛቤ ፈጠራ ስራዎች ተጠናክረው ቀጥለዋል ብለዋል።

የዘንድሮው የበልግ ዝናብ በአንዳንድ አካባቢዎች በአግባቡ ያልተዳረሰ በመሆኑ በተለይም የበቆሎ ምርት ላይ ችግር በመፍጠሩ በአጭር ጊዜ የሚደርሱ ሰብሎችን በመዝራት ለማካካስ ጥረት እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።

በክልሉ ለምግብ እጥረት ተጋላጭ የሆኑ አካባቢዎችን በመለየትም በሌማት ትሩፋትና ሌሎችም የግብርና ኤንሸቲቮች ምርታማ እንዲሆኑ እየተደረገ መሆኑን ጠቁመዋል።

የመጠባበቂያ እህል ክምችት አቅምን የማሳደግ እንዲሁም የሰብል ልማትና የመጠባበቂያ ፈንድ የማሰባሰብ ጥረት በተጠናከረ መልኩ መቀጠሉን ተናግረዋል።

በሲዳማ ህዝብ ዘንድ በሚታወቀው ''ፎጮ'' የተሰኘ ባህላዊ ስርአት አማካኝነት ያለው ለሌለው እህል የማሰባሰብ ልምድም ተግባራዊ እየሆነ ነው ብለዋል።

ለአደጋዎች ፈጣን ምላሽ ለመስጠት ከ200 ሚሊየን ብር በላይ የመጠባበቂያ ፈንድ መኖሩን የጠቀሱት ኮሚሽነሩ በተያዘው ዓመትም ተጨማሪ የመጠባበቂያ ፈንድ የማሰባሰብ ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል ሲሉ ተናግረዋል።

እንደ አጠቃላይ በሲዳማ ክልል የተፈጥሮና ሰው ሰራሽ አደጋዎችን በራስ አቅም የተቀናጀና ፈጣን ምላሽ መስጠት የሚያስችል አቅም እየተገነባ ይገኛል ብለዋል።

በባለፈው ክረምት የወንዝ ሙላት፣ ጎርፍና የመሬት መንሸራተት ያስከተለውን አደጋ መነሻ በማድረግ ለተመሳሳይ አደጋዎች በስጋት አካባቢ የሚኖሩ ወገኖችን ወደ ሌሎች አካባቢዎች የማስፈር ስራ መሰራቱን አንስተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026