🔇Unmute
አርባምንጭ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህዝቡ የልማት ጥያቄዎች እንዲመለሱ ውጤታማ የክትትልና የቁጥጥር ስራ ማከናወኑን ገለጸ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአርባምንጭ ከተማ እያካሄደ ነው።

የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላትን የስራ እንቅስቃሴ በመከታተልና በመቆጣጠር ውጤታማ ተግባር አከናውኗል።
የአስፈጻሚ አካላት የልማት እንቅስቃሴን በቋሚ ኮሚቴዎች በማስገምገምና በመስክ ስራ ክትትልና ድጋፍ ጠንካራ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል።

በበጀት ዓመቱ በክልሉ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማስመዝገብ፣ የህዝቡን የልማት ፍላጎት እንዲሁም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት መደረጉን አንስተዋል ።
በተለይም የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እንዲመለሱ የተደረገ ጥረት ውጤታማ መሆኑን አመልክተዋል።
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...
Jul 18, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...
Jun 24, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026