🔇Unmute
አርባምንጭ፤ ሐምሌ 17/2018 (ኢዜአ)፡- የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የህዝቡ የልማት ጥያቄዎች እንዲመለሱ ውጤታማ የክትትልና የቁጥጥር ስራ ማከናወኑን ገለጸ፡፡
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5ኛ ዓመት የስራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤውን በአርባምንጭ ከተማ እያካሄደ ነው።

የክልሉ ምክር ቤት ምክትል አፈ-ጉባኤ ወላይቴ ቢቶ በጉባኤው መክፈቻ ላይ ባደረጉት ንግግር ምክር ቤቱ የአስፈጻሚ አካላትን የስራ እንቅስቃሴ በመከታተልና በመቆጣጠር ውጤታማ ተግባር አከናውኗል።
የአስፈጻሚ አካላት የልማት እንቅስቃሴን በቋሚ ኮሚቴዎች በማስገምገምና በመስክ ስራ ክትትልና ድጋፍ ጠንካራ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል።

በበጀት ዓመቱ በክልሉ ሁለንተናዊ ዕድገት ለማስመዝገብ፣ የህዝቡን የልማት ፍላጎት እንዲሁም ኢኮኖሚያዊና ማህበራዊ ጥያቄዎችን ለመመለስ ከፍተኛ ጥረት መደረጉን አንስተዋል ።
በተለይም የህዝቡ የልማትና የመልካም አስተዳደር ጥያቄዎች ደረጃ በደረጃ እንዲመለሱ የተደረገ ጥረት ውጤታማ መሆኑን አመልክተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026