🔇Unmute
አርባ ምንጭ፤ ሐምሌ 17/2018(ኢዜአ)፦ በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የምግብ ሉዓላዊነትንና የኢንዱስትሪ ግብአትን መሰረት ያደረጉ የግብርና ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ውጤትም እየተመዘገበ መሆኑን የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር፣ 5ኛ ዓመት የሥራ ዘመን 7ኛ መደበኛ ጉባኤ በአርባ ምንጭ ከተማ እየተካሄደ ይገኛል።

የክልሉን መንግሥት የ2018 በጀት ዓመት አጠቃላይ የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ያቀረቡት ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ፤ ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ የምግብ ሉዓላዊነትን ለማረጋገጥና የህዝቡን ተጠቃሚነት ማረጋገጥ የሚያስችሉ የልማት ኢንሼቲቮች እየተተገበሩ መሆኑን ገልጸዋል።
በተለይም በሌማት ትሩፋት፣ በስንዴ ልማት እና በአረንጓዴ ዐሻራ መርሃ ግብር ከተፈጥሮ ሃብት ልማት ባለፈ የምግብ ዋስትናን በማረጋገጥ ሂደት የተመዘገበውን ስኬት ለአብነት ጠቅሰዋል።

በመሆኑም የምግብ ሉዓላዊነትንና የኢንዱስትሪ ግብአትን መሰረት ያደረጉ የግብርና ልማት ስራዎች በስፋት እየተከናወኑ ውጤትም እየተመዘገበባቸው ይገኛል ብለዋል።
በቱሪዝም እና የማዕድን ሃብት ልማት፣ መስኖ ልማትና በኩታ ገጠም እርሻ፣ የሌማት ትሩፋት እንዲሁም የአትክልትና ፍራፍሬ ልማት አስደናቂ ስኬት መመዝገቡን ጠቅሰዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026