የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ የተመዘገቡ ስኬቶች የክልሉን የመልማት አቅም ያረጋገጡ ናቸው - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ የተመዘገቡ ስኬቶች የክልሉን የመልማት አቅም ያረጋገጡ መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5 ዓመት 3ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት፤ በበጀት ዓመቱ ክልሉ በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ ናቸው።


በዋናነት የክልሉ የኢኮኖሚ ምሰሶ የሆነውን የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት በቤተሰብ ደረጃ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ያረጋገጠ ሲሆን የኢኮኖሚ አቅሙንም ማሳደግ አስችሏል ብለዋል።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ከ55 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን አመልክተው የመካናይዜሽን እርሻ ተግባራዊ በመደረጉ ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን ጠቅሰዋል።


በዚህም በሄክታር እስከ 34 ኩንታል ምርት ማግኝት ተችሏል ነው ያሉት በሪፖርታቸው።


በተጨማሪም ባለፉት ጥቂት ዓመታት መንግስት ለማዕድን ዘርፉ ትኩረት መስጠቱ ለክልሉ ተጨማሪ የኢኮኖሚ ምንጭ ከመሆኑ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ሰፊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።


ለአብነትም በበጀት ዓመቱ ዘርፉ ህጋዊ በሆነ መንገድ እንዲመራ በማድረግና አነስተኛ የማዕድን አምራቾችን ወደ ስራ በማስገባት ከ8 ሺህ 900 ኪሎግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ መቻሉን አስታውቀዋል።


በክልሉ ያለውን የልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን ለማድረግም የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በማዘመን የተሻለ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመላክተዋል።


በአጠቃላይ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶች የክልሉን የመልማት አቅም ያረጋገጡና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ በሪፖርታቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026