የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ የተመዘገቡ ስኬቶች የክልሉን የመልማት አቅም ያረጋገጡ ናቸው - ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አሶሳ፤ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡- በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በክልሉ የተመዘገቡ ስኬቶች የክልሉን የመልማት አቅም ያረጋገጡ መሆናቸውን የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን ገለጹ።


የቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ምክር ቤት 6ኛ ዙር 5 ዓመት 3ኛ የሥራ ዘመን 5ኛ መደበኛ ጉባኤውን ማካሄድ ጀምሯል።


የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር አሻድሊ ሀሰን የተጠናቀቀው በጀት ዓመት አፈጻጸም ሪፖርት ባቀረቡበት ወቅት እንደገለፁት፤ በበጀት ዓመቱ ክልሉ በሁሉም ዘርፎች የተከናወኑ የልማት እና የመልካም አስተዳደር ስራዎች ውጤታማ ናቸው።


በዋናነት የክልሉ የኢኮኖሚ ምሰሶ የሆነውን የግብርናውን ዘርፍ በማዘመን ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ የተከናወኑ ተግባራት በቤተሰብ ደረጃ የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ያረጋገጠ ሲሆን የኢኮኖሚ አቅሙንም ማሳደግ አስችሏል ብለዋል።


በተጠናቀቀው በጀት ዓመትም ከ55 ሚሊየን ኩንታል በላይ ምርት መገኘቱን አመልክተው የመካናይዜሽን እርሻ ተግባራዊ በመደረጉ ምርታማነትን ማሳደግ መቻሉን ጠቅሰዋል።


በዚህም በሄክታር እስከ 34 ኩንታል ምርት ማግኝት ተችሏል ነው ያሉት በሪፖርታቸው።


በተጨማሪም ባለፉት ጥቂት ዓመታት መንግስት ለማዕድን ዘርፉ ትኩረት መስጠቱ ለክልሉ ተጨማሪ የኢኮኖሚ ምንጭ ከመሆኑ ባለፈ ለሥራ ዕድል ፈጠራ ሰፊ አስተዋጽኦ ማበርከቱን ገልጸዋል።


ለአብነትም በበጀት ዓመቱ ዘርፉ ህጋዊ በሆነ መንገድ እንዲመራ በማድረግና አነስተኛ የማዕድን አምራቾችን ወደ ስራ በማስገባት ከ8 ሺህ 900 ኪሎግራም በላይ ወርቅ ለብሔራዊ ባንክ ማቅረብ መቻሉን አስታውቀዋል።


በክልሉ ያለውን የልማት ፍላጎት በራስ አቅም ለመሸፈን ለማድረግም የገቢ አሰባሰብ ሂደቱን በማዘመን የተሻለ ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አመላክተዋል።


በአጠቃላይ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የተመዘገቡ ስኬቶች የክልሉን የመልማት አቅም ያረጋገጡና የህብረተሰቡን ተጠቃሚነት ያሳደጉ መሆናቸውን ርዕሰ መስተዳድሩ በሪፖርታቸው ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026