የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በሸገር ከተማ በ2018 በጀት ዓመት በተከናወኑት የተለያዩ የልማት ስራዎች ህብረተሰቡን ተጠቃሚ ማድረግ ተችሏል

Jul 27, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሸገር፣ ሐምሌ 18/2018 (ኢዜአ)፡-በሸገር ከተማ ማሕበረሰቡን ተጠቃሚ ለማድረግ በ2018 በጀት ዓመት የተከናወኑ የልማት ስራዎች ስኬታማ መሆናቸውን የከተማዋ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር )ገለጹ።

የሸገር ከተማ የ2018 በጀት ዓመት የ4ኛው ሩብ ዓመት የክትትልና አስፈጻሚ አካላት የሥራ አፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ውይይት ተደርጎበታል።


የከተማዋ ከንቲባ ተሾመ አዱኛ (ዶ/ር ) ሪፖርቱንት ባቀረቡበት ወቅት እንዳሉት፤ በተጠናቀቀው በጀት ዓመት የከተማዋንና የማሕበረሰቡን ሁለንተናዊ ተጠቃሚነት ያረጋገጡ በርካታ ተግባራትን በማከናወን ከፍተኛ ውጤት ተመዝግቧል።

በተለይም የገቢ አቅምን ለማሳደግ በተከናወኑ ተግባራት ከፍተኛ ለውጥ መምጣቱን አንስተው፣ በ2018 በጀት ዓመት 40 ነጥብ 17 ቢሊዮን ብር ገቢ መሰብሰብ መቻሉን አስረድተዋል።

የተሰበሰበው ገቢ መሰረተ ልማቶችን በማስፋፋት ለማኅበረሰቡ የሚሰጠውን አገልግሎት ፈጣን፣ ተወዳዳሪና ዘመናዊ ለማድረግ የሚያስችል እንደሆነም ተናግረዋል።

የተገኘው ገቢ ከአምው ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር የ15 ነጥብ 8 ቢሊዮን ብር ብልጫ ያለው መሆኑንም ነው የጠቆሙት።

በበጀት ዓመቱ 348 የተለያዩ ፕሮጀክቶችን በማጠናቀቅ ለአገልግሎት ክፍት በማድረግ የሕብረተሰቡን ማኅበራዊና ኢኮኖሚያዊ ተጠቃሚነት ማረጋገጥ ተችሏል ነው ያሉት ።

በከተማዋ በትምህርት ዘርፍ የተተገበሩ ኢኒሼቲቮችም በትምህርት ቤቶች ቁጥር፣ በትምህርት ዕድልና ተደራሽነት ረገድ ከፍተኛ ውጤቶች ማስመዝገብ መቻሉን ነው የገለጹት።

በዚሁ መሠረት 121 የቅድመ መደበኛ እና 15 የ1ኛ ደረጃ ትምህርት ቤቶች መገንባታቸውን ነው ያመለከቱት።

ከዚህ በተጨማሪ የተማሪዎች ምገባ መርሃ ግብርም በ1 ሺህ 224 ትምህርት ቤቶች ውስጥ ተግባራዊ ሆነዋል፤በዚህም 382 ሺህ 176 ተማሪዎችን ተጠቃሚ ማድረግ የተቻለ መሆኑን አስረድተዋል።

በዚህም የተማሪዎችን መጠነ መቅረት ከማስቀረቱ ባለፈ የትምህርት ጥራትን ለማረጋገጥ ማገዙን አንስተዋል።

በሸገር ከተማም የጤና አገልግሎትን ተደራሽ ለማድረግ በተከናወኑ ተግባራትም ሶስት የሚደርሱ ሆስፒታሎችን አገልግሎት ማስጀመር መቻሉ አክለዋል።

በሕብረተሰብ አቀፍ የጤና መድህን በኩልም ከአንድ ሚሊዮን በላይ የቤተሰብ አባላትን ማቀፍ የተቻለ ሲሆን 609 ሺህ በላይ ዜጎች የሕክምና አገለግሎት ማግኘታቸውንም ነው የተናገሩት።

በተጠናቀቀው በበጀት ዓመት ንጹህ የመጠጥ ውሃን ተደራሽ በማድረግ 59 ነጥብ 9 በመቶ የነበረውን ሽፋን ወደ 71 በመቶ ለማሳደግ ተችሏል ነው ያሉት።

በዚህም 322 ሺህ በላይ የሚደርስ ሕዝብ ተጠቃሚ ማድረግ መቻሉን ገልጸዋል።

በሸገር ከተማ በ2018 በጀት ዓመት በመጀመሪያ ደረጃ እና በይግባኝ ሰሚ ፍርድ ቤቶች 8 ሺህ በላይ መዝገቦች እልባት አግኝተዋል ብለዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026