🔇Unmute
አርባምንጭ፤ ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ) ፡-በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ አሟጦ በመሰብሰብ የልማት ፍላጎትን ለማሟላት የተጀመሩ ጥረቶች ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የክልሉ ርእሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ ገለጹ።
የደቡብ ኢትዮጵያ ክልል ገቢዎች ቢሮ የ2018 በጀት ዓመት የዕቅድ አፈጻጸም እና የ2019 ዕቅድ ላይ ያተኮረ የምክክር ጉባኤ በአርባምንጭ ከተማ እየተካሄደ ነው።

የክልሉ ርዕሰ መስተዳድር ጥላሁን ከበደ በመድረኩ ላይ እንደገለጹት በክልሉ ኢኮኖሚው የሚያመነጨውን ገቢ በአግባቡ በመሰብሰብ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት እየተደረገ ባለው ጥረት ውጤት እየተገኘ ነው ።
በተያዘው የ2019 በጀት አመትም የክልሉን የገቢ አቅም ለይቶ በተደራጀ ህዝባዊ ንቅናቄ የግብር እቅድን ለማሳካት እንደሚሰራ ተናግረዋል።
በዚህም በበጀት አመቱ የታቀደውን 48 ነጥብ 2 ቢሊየን ብር የገቢ ዕቅድ ለማሳካት በትኩረት እንደሚሰራ አመላክተዋል።
የህግና የአሠራር ስርአት በመታገዝ የገቢ አቅምን በማስፋት የክልሉን ዕድገት ዘላቂነት በማረጋገጥ የህዝቡን የልማት ፍላጎት ለማሟላት በትኩረት እንደሚሠራ አስታውቀዋል።
የክልሉ ገቢዎች ቢሮ ሃላፊ ዓለምነሽ ደመቀ በበኩላቸው በተጠናቀቀው በጀት ዓመት በገቢ ራስን ለመቻል በተደረጉ ጥረቶች አመርቂ ውጤት ተመዝግቧል ብለዋል።

ባለፉት ዓመታት በየዓመቱ 7 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር የገቢ ዕድገት መመዝገቡን ጠቅሰው በተጠናቀቀው የበጀት ዓመት 32 ነጥብ 4 ቢሊየን ብር መሰብሰቡን ገልጸዋል።
ተቋማዊ የመፈጸም አቅም በማሳደግና ብልሹ አሠራርን በማስወገድ የገቢ ስራው በዲጅታል ቴክኖሎጂ በመታገዝ መሠራቱን ገልጸዋል።
በ2019 የበጀት ዓመት የክልሉን ወጪ 75 በመቶ በውስጥ አቅም ለመሸፈን የታቀደውን ግብ ለማሳካት በቅንጅት እንደሚሠራ የቢሮ ሃላፊዋ አመልክተዋል።
በመድረኩ የክልል፣ የዞንና የከተማ አስተዳደሮች የስራ ሃላፊዎችና የዘርፉ ባለሙያዎች ተሳትፈዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026