🔇Unmute
ወልቂጤ ፤ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ)፦ የወልቂጤ ከተማን የኮሪደር ልማት በተያዘለት ጊዜ በማጠናቀቅ ከተማዋን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።
የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በከተማዋ በሁለተኛው ዙር እየተገነባ ያለውን የ6 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡

በዚህም ከተማዋን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰው የኮሪደር ልማቱ ፋውንቴይን ፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያ፣ የእግረኛ መንገድ ፣ የልጆች መጫወቻን ጨምሮ ፕላዛዎችን አካቶ እየተገነባ ነው ብለዋል፡፡
ከመጀመሪያው ዙር ልምድ የተወሰደበት ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት በመንገድ ዳርቻ ያሉ የንግድ ተቋማትንም በአዲስ መልክ በመገንባት የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ሲሆን በለሙ ቦታዎችም የጥላ ዛፎች እየተተከሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከ70 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የኮሪደር ልማት ከ220 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተያዘለት ሲሆን እስከ ፊታችን ነሃሴ መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡
ከወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ሻምበል በደዊ መሃመድና አቶ ሃብታሙ እሸቱ እንደተናገሩት፤ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን እያደረጋት ነው።

በተለይም ከዚህ ቀደም የነበረውን የመንገድ ጥበት በመቅረፍ ከተማዋን ለኢንቨስትመንት ተመራጭና ተወዳዳሪ እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በኮሪደር ልማቱ የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ሲራክ ተመስገን በሰጠው አስተያየት፤ ልማቱ ሙያዊ አቅሙን ከማሻሻልና የስራ ባህልን ከመቀየር ባለፈ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዳደረገው ተናግሯል፡፡
አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...
Jul 18, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...
Jun 24, 2026
አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...
Jun 10, 2026
አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...
Jun 9, 2026