የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ወልቂጤ ከተማን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ ቀጥሏል

Jul 28, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ወልቂጤ ፤ሐምሌ 20/2018 (ኢዜአ)፦ የወልቂጤ ከተማን የኮሪደር ልማት በተያዘለት ጊዜ በማጠናቀቅ ከተማዋን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን የከተማው አስተዳደር አስታወቀ።

የወልቂጤ ከተማ ከንቲባ አቶ ሙራድ ከድር ለኢዜአ እንደገለፁት፤ በከተማዋ በሁለተኛው ዙር እየተገነባ ያለውን የ6 ነጥብ 8 ኪሎ ሜትር የኮሪደር ልማት በተያዘለት ጊዜ ለማጠናቀቅ ርብርብ እየተደረገ ነው፡፡


በዚህም ከተማዋን ለኑሮና ለኢንቨስትመንት ተመራጭ የማድረጉ ተግባር ተጠናክሮ መቀጠሉን ጠቅሰው የኮሪደር ልማቱ ፋውንቴይን ፣ የተሽከርካሪ ማቆሚያ፣ የእግረኛ መንገድ ፣ የልጆች መጫወቻን ጨምሮ ፕላዛዎችን አካቶ እየተገነባ ነው ብለዋል፡፡

ከመጀመሪያው ዙር ልምድ የተወሰደበት ሁለተኛው ዙር የኮሪደር ልማት በመንገድ ዳርቻ ያሉ የንግድ ተቋማትንም በአዲስ መልክ በመገንባት የከተማዋን ገጽታ እየቀየረ ሲሆን በለሙ ቦታዎችም የጥላ ዛፎች እየተተከሉ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከ70 በመቶ በላይ የተጠናቀቀው የኮሪደር ልማት ከ220 ሚሊየን ብር በላይ ወጪ የተያዘለት ሲሆን እስከ ፊታችን ነሃሴ መጨረሻ ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል፡፡

ከወልቂጤ ከተማ ነዋሪዎች መካከል ሻምበል በደዊ መሃመድና አቶ ሃብታሙ እሸቱ እንደተናገሩት፤ የኮሪደር ልማቱ የከተማዋን ገፅታ በመቀየር ለነዋሪዎቿ ምቹ እንድትሆን እያደረጋት ነው።


በተለይም ከዚህ ቀደም የነበረውን የመንገድ ጥበት በመቅረፍ ከተማዋን ለኢንቨስትመንት ተመራጭና ተወዳዳሪ እያደረጋት መሆኑን ተናግረዋል፡፡


በኮሪደር ልማቱ የስራ እድል ከተፈጠረላቸው ዜጎች መካከል ሲራክ ተመስገን በሰጠው አስተያየት፤ ልማቱ ሙያዊ አቅሙን ከማሻሻልና የስራ ባህልን ከመቀየር ባለፈ በኢኮኖሚ ተጠቃሚ እንዳደረገው ተናግሯል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026