የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የቡና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን ጥቅም ከፍ ለማድረግ ትኩረት ተሰጥቷል

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ሚዛን አማን፣ ሐምሌ 21/2018 (ኢዜአ):- በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል የቡና ልማትን በማስፋፋትና ምርታማነትን በማሳደግ ከዘርፉ የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጥቅም ከፍ ለማድረግ ትኩረት መሰጠቱን የክልሉ ቡና፣ ሻይና ቅመማ ቅመም ባለሥልጣን ገለጸ።

የባለሥልጣኑ ምክትል ዋና ዳይሬክተር አቶ በላይ ኮጁአብ ለኢዜአ እንዳሉት በክልሉ ከቡና የሚገኘውን ኢኮኖሚያዊ ጠቀሜታ ከፍ ለማድረግ ልማቱን የማስፋፋትና ምርታማነትን ማሳደግ ላይ ትኩረት ተሰጥቷል።


በዚህም በክረምቱ ወራት ከ25 ሚሊዮን በላይ የቡና ችግኞችን ለመትከል ወደስራ መገባቱን ተናግረዋል።

የቡና ልማቱን ለማሳካት ዝርያቸው የተሻሻሉና ለደጋና ቆላማ አየር ንብረት ተስማሚነታቸው በምርምር የተረጋገጡ ችግኞች ለአርሶ አደሩ መሰራጨታቸውን ጠቁመዋል።

የተሻሻሉ የቡና ዝርያዎችም በአንድ ዓመት ጊዜ ውስጥ ለምርት የሚደርሱ እና ከነባሩ የቡና ዝርያ በእጥፍ ምርት የሚሰጡ መሆናቸውን ጠቅሰው ልማቱን ለማሳካትም ሙያዊ ድጋፋና ክትትል እየተደረገ መሆኑን ተናግረዋል።


በሸካ ዞን የየኪ ወረዳ አርሶ አደር ሰሎሞን ብርሃኔ ከቡና የሚያገኙትን ተጠቃሚነት ለማሳደግ ያላቸውን የቡና ማሳ በየዓመቱ እያስፋፉ መሆኑን ገልጸዋል።

አምና ከወረዳው ያገኙትን አንድ ሺህ "ኬ1" የተሰኘ ምርጥ የቡና ችግኝ መትከላቸውንና ዘንድሮም ተግባሩን በማስቀጠል አንድ ሺህ ችግኞችን ለመትከል እየሰሩ መሆናቸውን ተናግረዋል።


ነባሩን የቡና ዝርያ በምርምር በተገኙ የቡና ዝርያዎች እየተኩ መሆናቸውን የተናገሩት ደግሞ አርሶ አደር ጢሞቴዎስ ከሮ እና ታደሰ እጅጉ ናቸው።

ቡናን ከማልማት ባሻገር ጥራቱን ለማስጠበቅ በግብርና ባለሙያ ትምህርት ታግዘው እየሠሩ መሆናቸውን አመልክተዋል።

ያላቸው ማሳ ላይ በየዓመቱ አዳዲስ ችግኞችን እየተከሉ የቡና ተጠቃሚነታቸውን ለማሳደግ ትኩረት መስጠታቸውን ገልጸዋል።

በደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ሕዝቦች ክልል 614 ሺህ ሄክታር መሬት በቡና እየለማ መሆኑ ታውቋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026