🔇Unmute
አዳማ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በምስራቅ ሸዋ ዞን በመኸር ወቅት እርሻው ከ20 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መታቀዱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለፀ።
የምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በ2018/19 የምርት ዘመን ከ20 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ ነው።

በዞኑ በዘንድሮው የመኸር ወቅት ለማልማት ታቅዶ ከነበረው ከ530 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ እስካሁን ከ475 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በተለያየ ምርጥ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል።
ለዚህም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር መዳበሪያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፣ እስካሁን ከ800 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ መቅረቡን ገልጸዋል።
የታቀደውን ምርት ለማግኘትም የግብርና ቴክኖሎጂ፣ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ በስፋት ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቅሰው፤ለአርሶ አደሩም ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።
የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የግብርና ምርቶችን የኤክስፖርት አቅም ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ በዕቅድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።
በዚህም የኤክስፖርት ምርቶችን ለመጨመር በስንዴ፣በቦሎቄና በሽንብራ ላይ በሜካናይዜሽን የተደገፈ የኩታ ገጠም የሰብል ልማት እየተከናወነ መሆኑንም አክለዋል።
የዞኑን ግብርና ከበሬ ማረስ በማውጣት ወደ ሜካናይዜሽን ለማሸጋገር በተያዘው ዓመት 155 የእርሻ ትራክተሮች ተገዝተው በልማት ስራ ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።
በዞኑ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ሽንብራ፣ ጤፍና ሌሎች ዋና ዋና ሰብሎች በ460 ክላስተር በመደራጀት እየለሙ መሆናቸውን ምክትል ኃላፊው አስረድተዋል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026