የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በምስራቅ ሸዋ ዞን በመኸር ወቅት እርሻ ከ20 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ይጠበቃል

Jul 29, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በምስራቅ ሸዋ ዞን በመኸር ወቅት እርሻው ከ20 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት መታቀዱን የዞኑ ግብርና ጽሕፈት ቤት ገለፀ።

የምስራቅ ሸዋ ዞን ግብርና ጽሕፈት ቤት ምክትል ኃላፊ አቶ አብነት ዘገየ ለኢዜአ እንደገለጹት፤ በዞኑ በ2018/19 የምርት ዘመን ከ20 ሚሊዮን ኩንታል በላይ ምርት ለማምረት ታቅዶ እየተሰራ ነው።


በዞኑ በዘንድሮው የመኸር ወቅት ለማልማት ታቅዶ ከነበረው ከ530 ሺህ ሄክታር በላይ መሬት ውስጥ እስካሁን ከ475 ሺህ ሄክታር በላይ የሚሆነው በተለያየ ምርጥ ዘር መሸፈኑን ተናግረዋል።

ለዚህም ምርትና ምርታማነትን ለማሳደግ 1 ነጥብ 2 ሚሊዮን ኩንታል የአፈር መዳበሪያ ለማቅረብ መታቀዱን ጠቅሰው፣ እስካሁን ከ800 ሺህ ኩንታል በላይ የአፈር ማዳበሪያ መቅረቡን ገልጸዋል።

የታቀደውን ምርት ለማግኘትም የግብርና ቴክኖሎጂ፣ምርጥ ዘርና የአፈር ማዳበሪያ በስፋት ጥቅም ላይ መዋሉን ጠቅሰው፤ለአርሶ አደሩም ሙያዊ ድጋፍና ክትትል እየተደረገ ነው ብለዋል።

የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥና የግብርና ምርቶችን የኤክስፖርት አቅም ለማሳደግ የሚደረገውን ጥረት ለመደገፍ በዕቅድ እየተሰራ መሆኑን ገልጸዋል።

በዚህም የኤክስፖርት ምርቶችን ለመጨመር በስንዴ፣በቦሎቄና በሽንብራ ላይ በሜካናይዜሽን የተደገፈ የኩታ ገጠም የሰብል ልማት እየተከናወነ መሆኑንም አክለዋል።

የዞኑን ግብርና ከበሬ ማረስ በማውጣት ወደ ሜካናይዜሽን ለማሸጋገር በተያዘው ዓመት 155 የእርሻ ትራክተሮች ተገዝተው በልማት ስራ ላይ እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

በዞኑ ስንዴ፣ ቦሎቄ፣ ሽንብራ፣ ጤፍና ሌሎች ዋና ዋና ሰብሎች በ460 ክላስተር በመደራጀት እየለሙ መሆናቸውን ምክትል ኃላፊው አስረድተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

ባለፉት አምስት ዓመታት አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ ተችሏል – ከንቲባ አዳነች አቤቤ

አዲስ አበባ፤ ሐምሌ 10/2018(ኢዜአ)፦ ባለፉት አምስት ዓመታት ስር የሰደዱ ችግሮችን በመቅረፍ አዲስ አበባን የሰላምና የልማት ማዕከል ማድረግ መቻሉን የአዲስ...

Jul 18, 2026

በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገበ ነው

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 16/2018 (ኢዜአ)፦ በኢትዮጵያ እየተተገበረ ያለው ሀገር በቀል የኢኮኖሚ ማሻሻያ በሁሉም ዘርፍ ለትውልድ የሚሻገር የላቀ ዕድገት እያስመዘገ...

Jun 24, 2026

የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ እያደረገ ነው 

አዲስ አበባ፤ሰኔ 2 /2018 (ኢዜአ)፦የዕቃ ማከማቻ ደረሰኝ ሥርዓት ደንብ የግብርና ኢኮኖሚ ሽግግርን በማሳለጥና የገጠር ልማትን በማጎልበት አርሶ አደሮችን ተጠ...

Jun 10, 2026

በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ተግባራት ተጠናክረው ቀጥለዋል

አዲስ አበባ፤ ሰኔ 1/2018 (ኢዜአ)፦ በመዲናዋ የመንግሥት አገልግሎት አሰጣጥን በማላቅ የተገልጋዮችን እርካታ የሚያሳድጉ ሰው ተኮር ተግባራት ተጠናክረው እንደ...

Jun 9, 2026