የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ይጠናከራሉ - ርዕሰ መስተዳድር ዓለሚቱ ኡሞድ

Sep 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጋምቤላ ፤ጳጉሜ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በክልሉ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።

ጳጉሜ 5 የነገ ቀን ’’የዲጂታል አብዮት ለነገዋ ኢትዮጵያ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በጋምቤላ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል።


ርዕሰ መስተዳድሯ ዕለቱን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግ የተጀመሩት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።

በመደመር እሳቤ ባለፉት ዓመታት በቴክኖሎጂ ዘርፍ በተከናወኑ ተግባራት እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።

የዲጂታል ኢኮኖሚውን ስኬታማ ለማድረግ በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና እና በሌሎችም የክልሉን ወጣቶች በማሳተፍ የዲጂታል ቴክኖሎጂውን ዘርፍ ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።

በተለይም የክልሉ ወጣቶች የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን በማዳበር በዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ጠንክረው ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።

በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን፣ የሳይበር ደህንነትንና የዳታ አስተዳደርን በማጠናከር ለዜጎች ቀልጣፋና የዘመነ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።

የዕለቱ በዓልም በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡትንና ለኢትዮጵያ ማንሰራራት መሰረት የጣሉ ስኬቶችን ለማብሰርና ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሯ ገልጸዋል።


የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊና የበዓሉ አስተባባሪ ኢንጂነር ጓነር ጆክ በዚሁ ጊዜ የነገ ቀንን ስናከብር በአዲስ ተስፋና ተነሳሽነት ሰው ተኮር አገልግሎቶችን ለማጠናከር መሆኑን ተናግረዋል።

በክብረ በዓሉ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የከተማው ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ ዕለቱን በማስመልከት የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026