🔇Unmute
ጋምቤላ ፤ጳጉሜ 5/2018 (ኢዜአ)፡- በክልሉ የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግ እየተከናወኑ ያሉ ተግባራት ተጠናክረው እንደሚቀጥሉ የጋምቤላ ክልል ርዕሰ መስተዳድር ወይዘሮ ዓለሚቱ ኡሞድ ገለጹ።
ጳጉሜ 5 የነገ ቀን ’’የዲጂታል አብዮት ለነገዋ ኢትዮጵያ’’ በሚል መሪ ሃሳብ በጋምቤላ ከተማ በፓናል ውይይት ተከብሯል።

ርዕሰ መስተዳድሯ ዕለቱን አስመልክተው ባስተላለፉት መልዕክት የዲጂታል ትራንስፎርሜሽን ስትራቴጂን ስኬታማ ለማድረግ የተጀመሩት ስራዎች ተጠናክረው ይቀጥላሉ ብለዋል።
በመደመር እሳቤ ባለፉት ዓመታት በቴክኖሎጂ ዘርፍ በተከናወኑ ተግባራት እንደ ክልልም ሆነ እንደ ሀገር በርካታ ውጤቶች መመዝገባቸውን አንስተዋል።
የዲጂታል ኢኮኖሚውን ስኬታማ ለማድረግ በኢትዮ-ኮደርስ ስልጠና እና በሌሎችም የክልሉን ወጣቶች በማሳተፍ የዲጂታል ቴክኖሎጂውን ዘርፍ ለማስፋት በትኩረት እየተሰራ ነው ብለዋል።
በተለይም የክልሉ ወጣቶች የቴክኖሎጂ ክህሎታቸውን በማዳበር በዲጂታል ኢኮኖሚው ግንባታ የበኩላቸውን ሚና ለመወጣት ጠንክረው ሊሰሩ እንደሚገባም አስገንዝበዋል።
በክልሉ መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎትን፣ የሳይበር ደህንነትንና የዳታ አስተዳደርን በማጠናከር ለዜጎች ቀልጣፋና የዘመነ አገልግሎት ለመስጠት የተጀመረው ጥረት ተጠናክሮ ይቀጥላል ብለዋል።
የዕለቱ በዓልም በለውጡ ዓመታት የተመዘገቡትንና ለኢትዮጵያ ማንሰራራት መሰረት የጣሉ ስኬቶችን ለማብሰርና ለማጠናከር ያለመ መሆኑን ርዕሰ መስተዳድሯ ገልጸዋል።

የክልሉ ስራና ክህሎት ቢሮ ኃላፊና የበዓሉ አስተባባሪ ኢንጂነር ጓነር ጆክ በዚሁ ጊዜ የነገ ቀንን ስናከብር በአዲስ ተስፋና ተነሳሽነት ሰው ተኮር አገልግሎቶችን ለማጠናከር መሆኑን ተናግረዋል።
በክብረ በዓሉ ላይ የክልሉ ከፍተኛ የስራ ኃላፊዎችና የከተማው ነዋሪዎች የተገኙ ሲሆን በመርሃ ግብሩ ላይ ዕለቱን በማስመልከት የመነሻ ጽሁፍ ቀርቦ በተሳታፊዎች ውይይት ተደርጎበታል።
ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...
Sep 10, 2026
ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...
Aug 13, 2026
ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...
Jul 30, 2026
ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...
Jul 30, 2026