የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

ዲጂታል ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ አገልግሎት አሰጣጥና የሥራ ዕድል እያሰፋ ነው

Sep 11, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጅግጅጋ፤ ጳጉሜን 5/2018 (ኢዜአ) ፦ዲጂታል ኢትዮጵያ የቴክኖሎጂ አጠቃቀምን በማሳደግ አገልግሎት አሰጣጥን እያቀላጠፈና የሥራ እድልን እያሰፋ መሆኑን የሶማሌ ክልል ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም ኡስማን ገለጹ።

የጳጉሜን 5 "የነገ ቀን" በሚል ስያሜ በተለያዩ የሀገሪቱ አካባቢዎች እየተከበረ ሲሆን በሶማሌ ክልል ደረጃም ቀኑ በጂግጂጋ ከተማ በተለያዩ ዲጂታል የንቅናቄ መርሃ-ግብሮች ተከብሯል።

በመርሃ-ግብሩ ላይ የክልሉ ምክትል ርዕሰ መስተዳድር አቶ ኢብራሂም እንደገለጹት፤ በክልሉ በቴክኖሎጂና በሰው ኃይል ልማት ላይ በስፋት በመስራት ሁለንተናዊ እድገትን በዘላቂነት ለማስመዝገብ እየተሰራ ነው።

በተለይ ዲጂታል አገልግሎትን በማስፋፋት ለአገልግሎት አሠጣጥ፣ ለሥራ ዕድል ፈጠራና ለክልሉ የኢኮኖሚ አቅም መጠናከር ትኩረት ተሰጥቶ በመሰራቱ አበረታች ውጤቶች ተገኝቷል ብለዋል።

ዲጂታል ኢትዮጵያን ማረጋገጥ በቴክኖሎጂ፣ በፋይናንስ፣ በትራንስፖርትና በሌሎችም ዘርፎች አሰራርን በማዘመን ለቀጣይ ትውልድ የተሻለች ሀገር ለማስረከብ ከፍተኛ ድርሻ እንዳለውም አስረድተዋል።


ለዚህም ስኬት የተቋማት የማስፈጸም አቅምን መገንባት አስፈላጊ መሆኑን ገልጸው፣ በክልሉ ተቋማትን በቴክኖሎጂ አቅርቦትና በሰው ኃይል የማደራጀት ሥራው ትኩረት እንደተሰጠው ገልጸዋል።

ለአብነትም በክልሉ የመንግሥት አገልግሎቶችን ለማቀላጠፍ 13 መሶብ የአንድ ማዕከል አገልግሎት መስጫዎች መገንባታቸውን ጠቁመዋል።

ምክትል ርዕሰ መስተዳድሩ እንዳሉት መንግሥት ለዲጂታል መሠረተ ልማት ግንባታ ዘርፍ የሠጠው ልዩ ትኩረት የነገን የሀገሪቱን አድገት ለማፋጠን የሚያግዝ ነው።

በዲጂታል ዘርፍ የኢትዮ ኮደርስ፣ የስታርትአፕ እና የዲጂታል ክህሎት ንቅናቄዎች የዜጎችን አቅም በመገንባት ረገድ ምቹ ሁኔታ እየፈጠሩ ይገኛሉ ሲሉም ገልጸዋል

የክልሉ ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ ቢሮ ኃላፊ አቶ መሀመድ አሊ በበኩላቸው እንዳሉት ፤ በክልሉ የዲጂታልና የፈጠራ ክህሎትን ለማዳበር ዘርፈ ብዙ ሥራዎች እየተከናወኑ ይገኛሉ።


በተለይም በክልሉ በስፋት እየተሰጠ ያለው የ“ኢትዮ ኮደርስ” ሥልጠና የወጣቶችን ቴክኖሎጂ የመጠቀም አቅም በከፍተኛ ደረጃ እያሳደገው መሆኑን ተናግረዋል።

ይህም ቴክኖሎጂን ጥቅም ላይ በማዋል የመንግሥትን አገልግሎቶች ለማዘመን ፣ የስራ ዕድል ለመፍጠርና የሀገርን ልማት በማፋጠን በኩል ከፍተኛ ሚና እንደሚኖረው አስገንዝበዋል።


በጅግጅጋ ከተማ በተካሄደው በዚህ መርሃ - ግብር ላይ የክልሉ ከፍተኛ የሥራ ኃላፊዎች፣ ባለድርሻ አካላት፣ ጥሪ የተደረገላቸው እንግዶች፣ ወጣቶችና የተለያዩ የሕብረተሰብ ክፍሎች ተገኝተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026