የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

የኢትዮጵያና እስራኤል ትብብር ወደ ላቀ ምዕራፍ ተሸጋግሯል-አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ (ዶ/ር)

Sep 18, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤መስከረም 6/2019 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያና እስራኤል ሁሉን አቀፍ ትብብር መጠናከር የሀገራቱን ግንኙነት ወደ ላቀ ምዕራፍ ማሸጋገሩን በእስራኤል የኢትዮጵያ አምባሳደር አብርሃም ንጉሴ (ዶ/ር) ገለጹ።

አምባሳደሩ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤የሁለቱ አገራት ግንኙነት ጥልቅ ታሪካዊ መሠረት ያለው መሆኑን ገልጸዋል።

ግንኙነቱ አሁን ላይ በመንግሥታት ትብብር፣በኢንቨስትመንት፣በቴክኖሎጂ እና በሰዎች አቅም ግንባታ ላይ የተመሠረተ ሁሉን አቀፍና ዘመናዊ አጋርነት ላይ መድረሱን አመልክተዋል።

ኢትዮጵያ እና እስራኤል ከጥንት ጀምሮ የነበራቸው ልዩ ታሪካዊ ግንኙነት ዛሬ ለደረሰበት ጠንካራ የሁለትዮሽ አጋርነት እንዳበቃቸው ተናግረዋል።

በአዲስ አበባ የሚገኘው የእስራኤል ኤምባሲ የሁለቱን አገራት የረጅም ጊዜ ግንኙነት ለማጠናከርና ለማስፋት በተለያዩ ዘርፎች በስፋት እየተንቀሳቀሰ መሆኑን አስረድተዋል።

የሁለቱ አገራት አበይት የትብብር መስኮች አንዱ የሆነው ግብርና፤ የእስራኤል ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ኩባንያዎችን በመገንባት ዘመናዊ የግብርና ቴክኖሎጂዎችንና ባለሙያዎችን ወደ ሀገር ውስጥ እንዲያስገቡ መልካም አጋጣሚን መፍጠሩን ነው ያነሱት።

የእስራኤል ኩባንያዎች በፍራፍሬና በአትክልት ልማት ላይ የተሰማሩባቸውን በቢሾፍቱ አካባቢ የሚገኙ የግብርና ስራዎች በማሳያነት ጠቅሰዋል።

በዘርፉ ያለው ትብብርና ኢንቨስትመንት ኢትዮጵያ አቮካዶን ጨምሮ የግብርና ምርቶቿን ወደ አውሮፓ እና እስያ ገበያዎች የምታቀርብበትን አቅም እንዲያድግ አስተዋጽኦ አድርጓል ብለዋል አምባሳደር አብርሃም።

በተጨማሪም የኢትዮጵያ ማክሮ ኢኮኖሚ ማሻሻያ ለውጭ ባለሀብቶች፣ እስራኤላውያንን ጨምሮ ምቹ ሁኔታዎችን እየፈጠረ መሆኑን አመልክተዋል።

የውጭ ባለሀብቶችን በመሳብ ረገድ የማክሮ ኢኮኖሚ ሪፎርሙ ከፍተኛ ጠቀሜታ እንዳለው የገለጹት አምባሳደሩ፤ የተደረጉት ማሻሻያዎች ባለሀብቶች በኢትዮጵያ ስራ ለመጀመር እና የኢንቨስትመንት ዕድሎችን ለመመልከት እያገዟቸው እንደሚገኙ ተናግረዋል።

የማዕድን አቅምን ጨምሮ የኢትዮጵያ ተፈጥሮ ሀብቶች ተጨማሪ የእስራኤል ኢንቨስትመንቶችን መሳብ የሚያስችሉ መሆናቸውን ነው ያስረዱት።

የእስራኤል ኩባንያዎች ወርቅን ጨምሮ በተለያዩ ማዕድናት ፍለጋና ማምረት ስራዎች ላይ ተሰማርተው እንደሚገኙ ጠቁመዋል።

ጤና ሁለቱ አገራት ትብብራቸውን እያሰፉባቸው ካሉ ዘርፎች መካከል አንዱ መሆኑን የገለጹት አምባሳደሩ፤ የእስራኤል ሀኪሞች ከኢትዮጵያ የህክምና ባለሙያዎች ጋር በመቀናጀት የአቅም ግንባታን ጨምሮ በተለያዩ መርሃ ግብሮች ላይ በትብብር እየሰሩ መሆናቸውን ገልጸዋል።

በኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መስኮች፣በተለይም በሳይበር ደህንነት ዙሪያ ያለውን ትብብር አምባሳደሩ አንስተዋል።

እስራኤል የሳይበር ደህንነት ተግዳሮቶችን በመቅረፍ ረገድ ያከማቸችውን ልምድ ለኢትዮጵያ ለማካፈል እንደምትሻም ተናግረዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026