የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በክልሉ ተቋማት ላይ ተግባራዊ የተደረገው የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተገልጋይን እርካታ እያረጋገጠ ነው

Sep 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ባህር ዳር፤ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ):- በአማራ ክልል ተቋማት ላይ ተግባራዊ የተደረገው የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የተገልጋይን እርካታ እያረጋገጠ መሆኑ ተገለፀ።

በክልሉ በመጀመሪያው ዙር ወደ መንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር ሪፎርም የገቡ ስምንት ተቋማት የሥራ አፈጻጸም ግምገማ መድረክ ተካሄዷል።


በአማራ ክልል በምክትል ርዕሰ መስተዳድር ማዕረግ የከተሞች ክላስተር አስተባባሪና የክልሉ ሪፎርም አብይ ኮሚቴ ሰብሳቢ አሕመዲን መሐመድ (ዶ/ር) በበኩላቸው፤ ሪፎርሙ የመንግሥት አገልግሎትና አስተዳደር የተገልጋይን እርካታ እያረጋገጠ መምጣቱን ገልጸዋል።

ይህም የመንግሥትን ተቋማት ነፃና ገለልተኛ እንዲሆኑ ከማድረግ ባሻገር የሠራተኛውን ችሎታና ብቃት ለማረጋገጥ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በተቋማት በቴክኖሎጂ የታገዘ የዲጂታል አሠራርን እውን በማድረግ ፈጠራና ፍጥነት የታከለበት አገልግሎትን በፍትሐዊነት ተደራሽ መሆኑ ውጤት እያስገኘ ነው ያሉት።

በተለይም የመሶብ አንድ ማዕከል አገልግሎት ፈጣንና ዘመናዊ አገልግሎት ተደራሽ ማድረግ ማስቻሉን ጠቅሰው፤ በዚህም በስድስት ማዕከላት በተሰጠ አገልግሎት የተገልጋይ እርካታን 99 ነጥብ 7 በመቶ ማድረስ እንደተቻለም ገልጸዋል።


የክልሉ ሲቪል ሰርቪስና ሰው ሀብት ልማት ቢሮ ኃላፊ ወይዘሮ ባንችአምላክ ገብረማርያም በበኩላቸው፤ ሪፎርሙ የመንግሥትን አገልግሎትና አስተዳደር በውጤታማነት ተደራሽ ለማድረግ የሚያስችል ነው ብለዋል።

በተለይም ከዚህ ቀደም በተቋማት ይስተዋሉ የነበሩ የሕዝብ አገልግሎት አሰጣጥ ችግሮችን በዘላቂነት በመፍታት ወጪ ቆጣቢ በሆነ አግባብ ውጤታማ ተግባራትን ማከናወን ማስቻሉን ጠቁመዋል።

ሪፎርሙ አሠራሮችን ዲጂታል በማድረግ ሥራን የማቅለልና የማዘመን ብሎም ብቁና ተወዳዳሪ የሰው ኃይል መገንባትን ዓላማ ያደረገ መሆኑን ጠቅሰዋል።

እስካሁን በተደረገ ጥረት ተቋማትን ለአሠራር ምቹ ከማድረግ ባለፈ የሕግ ማዕቀፎችን፣ ስትራቴጂዎችን፣ ደንቦችንና መመሪያዎችን በማዘጋጀት ወደ ሥራ መገባቱን ገልጸዋል።

በክልል ደረጃ 69 ተቋማት 361 አገልግሎቶቻቸውን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ከ183 ሺህ 300 በላይ ደንበኞች ቀልጣፋ አገልግሎት እንዲያገኙ ተደርጓል ብለዋል።

በሪፎርሙ የግዥ፣ የንብረት አስተዳደርና የክፍያ ሥርዓትን ዲጂታላይዝድ በማድረግ ውጤታማ ሥራ መከናወኑን ጠቅሰው፤ የገቢ ሥርዓቱን ከማኑዋል ወደ ዲጂታል በማሳደግ ገቢ የመሰብሰብ አቅም ከፍ እንዲል ማድረጉን አብራርተዋል።

ትምህርት፣ ጤና፣ ግብርና፣ ፕላንና ልማት እና ሥራና ክህሎት ቢሮዎች ሪፎርሙን በመተግበር የተሻለ ሥራ ማከናወናቸውን ተናግረዋል።

የተገኙ ውጤቶችን በማጠናከርም በየደረጃው የተሻለ ግንዛቤ ተፈጥሮ ወደ ተሟላ አፈጻጸም ለመግባት በቅንጅት መረባረብ እንደሚገባም አሳስበዋል።

በመድረኩ በሪፎርሙ ወደ ተግባር የገቡ ተቋማት አመራሮች የተሳተፉ ሲሆን የየተቋማቱ የሪፎርም አፈጻጸም ግምገማ ተካሄዷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026