የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ኢኮኖሚ እና ኢንቨስትመንት

በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል የአርሶ አደሩ በመስኖ የማልማት አቅም እየተገነባ ነው

Sep 20, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጂንካ፤ መስከረም 9/2019 (ኢዜአ)፡- በደቡብ ኢትዮጵያ ክልል አርሶ አደሩን ከዝናብ በተጨማሪ በመስኖ ዓመቱን ሙሉ የማምረት አቅም እየተገነባ መሆኑን የክልሉ መስኖና ቆላማ አካባቢ ልማት ቢሮ ገለጸ።


በክልሉ በአሪ ዞን ሰሜን አሪ ወረዳ ከ58 ሚሊዮን ብር በላይ በሆነ ወጪ ለመስኖ አገልግሎት የተጠለፈው ''የሳላ'' ወንዝ ዛሬ ተመርቆ ለአገልግሎት ክፍት ሆኗል።

የመስኖ ፕሮጀክቱ ከ80 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከሁለት መቶ በላይ አርሶ አደሮችን ተጠቃሚ ያደርጋል።

በወቅቱም የቢሮው ኃላፊ አቶ ኤካል ነትር እንዳሉት፣ የአካባቢውን አርሶ አደሮች ከክረምት ዝናብ በተጨማሪ በበጋ መስኖ ለማልማት የሚያስችላቸው ዕድል ተፈጥሯል።


የአርሶ አደሩን የምግብ ዋስትና ለማረጋገጥ እና የኢኮኖሚ አቅሙን ለማሳደግ የመስኖ አውታሮችን የማስፋፋት ሥራ የክልሉ መንግሥት በትኩረት እየሠራ መሆኑን አንስተዋል።

በሣላ ወንዝ የተሠራው አነስተኛ የመስኖ ፕሮጀክት አርሶ አደሩን ከክረምት ዝናብ ጥገኝነት ለማላቀቅ የሚደረገው ጥረት አካል መሆኑን ገልጸው በዚህም የአርሶ አደሩን በመስኖ የማልማት አቅም እየተገነባ መሆኑን አስረድተዋል።

ለአገልግሎት ክፍት የሆነው የመስኖ ፕሮጀክት የአካባቢው አርሶ አደሮች በቤተሰብ ደረጃ የምግብ ዋስትናቸውን ለማረጋገጥና የገቢ አቅማቸውን ለማሳደግ እንደሚረዳ ተናግረዋል።

የሣላ የመስኖ ፕሮጀክት በሥርዓተ ምግብ ማጠናከሪያ ፕሮግራም የተገነባ ሲሆን፣ ከ80 ሄክታር በላይ መሬት በማልማት ከሁለት መቶ በላይ አርሶ አደሮችና ቤተሰቦቻቸውን በቀጥታ ተጠቃሚ ያደርጋል ነው ያሉት።


የሰሜን አሪ ወረዳ ዋና አስተዳዳሪ ጎሳዬ ጉሳሬ በበኩላቸው፣ በወረዳው የሳላ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክትን ጨምሮ ሌሎች የመስኖ ልማት ስራዎችን በማዘመንና ምርትና ምርታማነትን በመጨመር የአርሶ አደሩ ሕይወት እየተለወጠ ነው ብለዋል።

የአሪ ዞን ዋና አስተዳዳሪ ተወካይ አቶ አፌዶ ወርቁ በበኩላቸው፣ መንግሥት የአርሶና የአርብቶ አደሩን ሕይወት በዘላቂነት ለመለወጥ እና የምግብ ዋስትናን ለማረጋገጥ በትኩረት እየሠራ መሆኑን ገልጸዋል።


አርሶ አደሮቹ መንግሥት በፈጠረላቸው ዕድል በመጠቀም ኑሯቸውን ለመለወጥ መትጋት እንዳለባቸው አሳስበው፤ የመስኖ አውታሩ በደለል እንዳይሞላ መጠበቅና መንከባከብ እንዳለባቸውም አመልክተዋል።

ከአካባቢው አርሶ አደሮች መካከል አቶ ንጋቱ ፀጋዬ እና አቶ ፌታ ጊዲፎ፣ የሳላ ወንዝ መስኖ ፕሮጀክት ለአርሶ አደሩ ዓመቱን ሙሉ በምርት ሥራ ላይ ተሰማርተው እንዲቆዩ ትልቅ ዕድልን እንደፈጠረላቸው ተናግረዋል።


ቀደም ሲል የግብርና ሥራዎቻቸው በዝናብ ላይ ብቻ ጥገኛ በመሆኑ ውስን ሰብሎችን ብቻ በማልማት ከእጅ ወደ አፍ የሆነ ኑሮ ይመሩ እንደነበር ጠቅሰው፣ አሁን በአካባቢው ለመስኖ አገልግሎት የሚውል ወንዝ በመጠለፉ ዓመቱን ሙሉ ማልማት የሚችሉበት አቅም መፈጠሩን ገልጸዋል።


በመርሐ ግብሩ ላይ የክልሉ እና የአሪ ዞን የመንግሥት የሥራ ኃላፊዎች፣ የአካባቢው የሀገር ሽማግሌዎች እና ተጋባዥ እንግዶች ታድመዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል በቂ የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶች ቀርበዋል

ባህር ዳር ፤ ጳጉሜን 4/2018 (ኢዜአ) ፦ በአማራ ክልል ለዘመን መለወጫ በዓል የእርድ እንስሳትና ሌሎች ምርቶችን በበቂ መጠን ለተጠቃሚው ማቅረብ መቻሉን የክ...

Sep 10, 2026

የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ በድሬዳዋ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ ነው

ድሬደዋ፤ ነሐሴ 6/2018 (ኢዜአ)፦ የኢትዮጵያ ታምርት ንቅናቄ አምራች ኢንዱስትሪዎችን ውጤታማ እያደረገ መሆኑን የድሬዳዋ አስተዳደር ምክትል ከንቲባ ሀርቢ ቡህ...

Aug 13, 2026

በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ ናቸው

ሮቤ፣ሐምሌ 22/2018(ኢዜአ)፦በባሌ ዞን በግብርናው ዘርፍ እየተከናወኑ የሚገኙ የልማት ሥራዎች በተሞክሮነት የሚወሰዱ መሆናቸውን የብልጽግና ፓርቲ የህዝብና ዓለ...

Jul 30, 2026

በክልሉ በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ ስራዎች ተከናውነዋል-ርዕሰ መስተዳድር እንዳሻው ጣሰዉ (ዶ/ር)

ሆሳዕና ፤ ሐምሌ 22/2018 (ኢዜአ)፦ በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት አመት በሰላም፣ በልማትና መልካም አስተዳደር የህዝቡን ተጠቃሚነት ያረጋገጡ...

Jul 30, 2026