የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

<p>በአማራ ክልል የኮደርስ ስልጠና ፕሮጀክትን ማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ ይገኛሉ - የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ</p>

Feb 6, 2025

IDOPRESS

ጎንደር፤ ጥር 21/2017(ኢዜአ)፡- በአማራ ክልል እየተከናወነ የሚገኘው የኢትዮ ኮደርስ የስልጠና ፕሮጀክትን ማሳካት የሚያስችሉ ተግባራት በመከናወን ላይ መሆናቸውን የአማራ ክልል ስራና ስልጠና ቢሮ ገለጸ።

በክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መርሃ ግብር የ6 ወራት የስራ አፈጻጸም የግምገማ መድረክ በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ተካሂዷል፡፡

በጎንደር ከተማ በተካሄደው በዚሁ መድረክ የተገኙት የክልሉ ስራና ስልጠና ቢሮ ምክትል ሀላፊ አቶ አማረ አለሙ እንደተናገሩት፤ ፕሮጀክቱ ወጣቶች የዲጂታል ቴክኖሎጂ ክህሎትና እውቀት በማዳበር ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን ከፍ የሚያደርግ ነው፡፡


ይህም እውቀትና ክህሎትን በማስታጠቅና በማብቃት ዘመኑን የዋጀ ትውልድ መገንባት ላይ ትኩረት ያደረገ መሆኑን ገልጸዋል።

በክልሉ በተያዘው በጀት ዓመት ዜጎችን የፕሮጀክቱ ተጠቃሚ ለማድረግ ታቅዶ እየተሰራ መሆኑን አመልክተው፤ ከ205 ሺህ በላይ ለሚሆኑ ወጣቶችና ለሌሎችም የህብረተሰብ ክፍሎች የግንዛቤ ፈጠራ ስራ መከናወኑን ጠቅሰዋል፡፡

ስልጠናውን የሚከታተሉ ሰልጣኞች 45ሺህ መድረሳቸውን ጠቁመው፤ ከ23ሺህ በላይ የሚሆኑት ስልጠናቸውን አጠናቀው ዓለም አቀፍ እውቅና ያለው ሰርቲፊኬት መቀበለቻውን አስረድተዋል።

ስልጠናው በዌብ ፕሮግራሚንግ፣ በአንድሮይድ ማበልፀግ፣ በዳታ ሳይንስና በአርቲፊሻል ኢንተለጀንስ መሠረታዊ የዲጂታል ክህሎትና ብቃት በማሳደግ ዓለም አቀፍ ተወዳዳሪነታቸውን የሚያሳድግ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

በክልሉ በቀጣዮቹ ሦስት ዓመታት ተደራሽ ለማድረግ ለተያዘው ዕቅድ ስኬታማነት አቅጣጫ ተቀምጦ እየተሰራ መሆኑን ጠቁመው፤ በየደረጃው ያለ የአመራር አባል ተልዕኮዎችን ተቀብሎ በመፈጸም ለፕሮጀክቱ መሳካት እንዲረባረብ መልዕክት አስተላልፈዋል።

በማዕከላዊ ጎንደር ዞን ፕሮጀክቱን የሚከታተልና የሚደግፍ አንድ ዐቢይ እና የቴክኒክ ከሚቴዎች ተዋቅረው ስልጠናውን ለማሳካት እየሰራ ነው ያሉት የዞኑ አስተዳደር ተወካይ አቶ ዳንኤል ወርቁ ናቸው፡፡

ኢትዮ ኮደርስ የወጣቶችን የዲጂታል ቴክኖሎጂ የአስተሳሰብ አድማስ ማስፋትና ማጎልበት የሚያስችል አለም አቀፍ ኢኒሼቲቭ መሆኑን ጠቁመው፤ የዲጂታል ክህሎት ስልጠና መርሃ ግብሩ እንዲሳካ የአመራር አባላት በትኩረት እየሰሩ እንደሚገኙ ገልጸዋል፡፡

የማዕከላዊ ጎንደር ዞን ስራና ስልጠና መምሪያ ሃላፊ አቶ እዮብ አግማስ በበኩላቸው፤ በዞኑ የስልጠና ማዕከላት ተቋቁመው በ92 የስልጠና አመቻቾች መርሃ ግብሩ እየተከናወነ ነው ብለዋል።

በበጀት ዓመቱ የስልጠና ዕድሉ ተጠቃሚ ለማድረግ ከታቀደው ውስጥ እስካሁን 5ሺህ 280 ስልጠና መውሰዳቸውን አስታውቀዋል፡፡

በመድረኩ በየደረጃው ያሉ አመራር አባላት በተገኙበት የስድስት ወራት የአፈጻጸም ሪፖርት ቀርቦ ተገምግሟል።

በጠቅላይ ሚኒስትር ዐቢይ አሕመድ(ዶ/ር) አነሳሽነት በኢትዮጵያና በተባበሩት አረብ ኤምሬትስ መንግስታት ትብብር የ"አምስት ሚሊዮን ኮደርስ" መርሃ ግብር በመላ ሀገሪቱ እየተተገበረ ይገኛል፡፡

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026