የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

በክልሉ በሚቀጥሉት አራት ወራት 50 ሺህ ወጣቶችን በኢትዮ ኮደርስ ለማሰልጠን ይሰራል

May 6, 2025

IDOPRESS

ቦንጋ፤ ሚያዝያ 21/2017 (ኢዜአ)፡-በቀጣይ አራት ወራት 50 ሺህ ወጣቶች የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለመስጠት እንደሚሰራ የደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ህዝቦች ክልል ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ግዛው ጋግያብ ገለፁ።

ቢሮው ለክልሉ ወጣት ክንፍ አመራሮች ስልጠናውን በማስመልከት የግንዛቤ ማስጨበጫ ስልጠና ሰጥቷል።


የክልሉ ኢንዱስትሪና ኢኖቬሽን ቢሮ ሀላፊ አቶ ግዛው ጋግያብ በወቅቱ እንዳሉት በክልሉ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግ የተለያዩ ኢንሼቲቮች ተቀርፀው እየተተገበሩ ይገኛሉ።

በዲጅታል ኢኮኖሚ የወጣቶችን ተጠቃሚነት ለማሳደግም የ5 ሚሊዮን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና ለክልሉ ወጣቶች በመስጠት የዕድሉ ተጠቃሚ ለማድረግ እየተሰራ መሆኑንም ተናግረዋል።

በተያዘው ዓመት በክልሉ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናን ለመውሰድ ከተመዘገቡ ከ11ሺህ በላይ ወጣቶች መካከል ከ8 ሺህ 400 በላይ ወጣቶች በአሁኑ ወቅት ስልጠና ላይ መሆናቸውን ገልጸዋል።

የግንዛቤ እጥረት፣ በአንዳንድ አካባቢዎች የኢንተርኔት ችግርና ቅንጅታዊ አሰራር አለመጠናከር በዓመቱ ለማሰልጠን በተያዘው ዕቅድ ላይ አሉታዊ ተጽዕኖ ማሳደሩን አመልክተዋል።

በቀጣይ አራት ወራት የግንዛቤ ችግሩን በመፍታትና ቅንጅታዊ አሰራርን በማጠናከር 50ሺህ ወጣቶችን መዝግቦ ለማሰልጠን በንቅናቄ እንደሚሰራም አስታውቀዋል።


በመድረኩ የተገኘው የክልሉ ብልፅግና ፓርቲ ወጣቶች ክንፍ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወጣት ሰይድ ኢብራሂም በበኩሉ እንደገለጸው፣ እንደሀገር የዲጂታል ኢኮኖሚን ለመገንባት እየተደረገ ባለው ጥረት ውስጥ ወጣቱ ግንባር ቀደም ተሰላፊና ተጠቃሚ መሆን አለበት።

የተጀመረው የ5 ሚሊዮን የኢትዮ ኮደርስ ስልጠናም ለወጣቱ ትልቅ እድል ይዞ በመምጣቱ የወጣት ክንፍ አመራሮች ለስልጠናው መሳካት ሀላፊነታቸውን ሊወጡ ይገባል ብለዋል።



የቦንጋ ከተማ አስተዳደር የብልፅግና ፓርቲ ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤት ሀላፊ ወጣት ታሪኩ አለማየሁ፣ ስልጠናው ያለውን ፋይዳ ለወጣቶች በማስገንዘብ የዕድሉ ተጠቃሚ ለማድረግ እንደሚሰራ ተናግሯል።

በመድረኩ ላይ የፌደራል ወጣት ክንፍ አባላት፣ የክልል ሥራ አስፈፃሚ፣ የዞን፣ የወረዳና የከተማ አስተዳደር የወጣት ክንፍ አመራሮች ተሳትፈዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026