
አዲስ አበባ፤ግንቦት 16/2017 (ኢዜአ)፦ክልሎች የኤሌክትሮኒክ ግዥ ሥርዓትን ተግባራዊ ለማድረግ ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ አስታወቁ።
የመንግስት ግዥና ንብረት ባለስልጣን ዋና ዳይሬክተር መሰረት መስቀሌ ከኢዜአ ጋር ባደረጉት ቆይታ፤ የኤሌክትሮኒክስ የመንግስት ግዥ ስርዓት በ169 የፌዴራል ተቋማትና በ93 ቅርንጫፍ ጽህፈት ቤቶቻቸው ተግባራዊ ተደርጓል።
በአገር አቀፍ ደረጃ ስርዓቱን ተግባራዊ ለማድረግ ክልሎችም ዝግጅት እያደረጉ መሆኑን አመልክተው፤ አዲስ አበባ ከተማ ወደ ሥርዓቱ ገብቶ ተግባራዊ እያደረገ መሆኑን አመልክተዋል።
ኦሮሚያ ክልል ዝግጅቱን ጨርሶ ሥልጠና በመስጠት ሂደት ላይ እንደሚገኝ አመልክተው፤ የድሬዳዋ አስተዳደር፣ ሶማሌ ክልል፣ ደቡብ ኢትዮጵያ ክልል፣ደቡብ ምዕራብ ኢትዮጵያ ክልል እና ማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልሎች ለ2018 ዓ.ም የግዥ ሥርዓታቸውን በኤሌክትሮኒክ ለመፈጸም የዝግጅት ሥራዎች እያከናወኑ እንደሚገኙ አመልክተዋል።
በበጀት አመቱ ሁሉም የፌደራል ተቋማት የግዥ እቅዶቻቸውን በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት ማቀዳቸውን ተናግረው፤ ይህም ትልቅ ውጤት የተገኘበት ነው ብለዋል።
በበጀት ዓመቱ ዘጠኝ ወራት ብቻ በኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት 533 ነጥብ 5 ቢሊየን ብር ግምት ያላቸው ግዥዎች በኤሌክትሮኒክስ ስርዓት መፈጸማቸውን ዋና ዳይሬክተሯ አንስተዋል።
ስርዓቱ ለግዥ የሚወጣውን ወጪና ጊዜ ከመቆጠብ እንዲሁም የሰነዶች ማጭበርበርን ከማስቀረት አኳያ ከፍተኛ ጠቀሜታ ማስገኘቱን ተናግረዋል።
በስርዓቱ አተገባበር ላይ ግንዛቤ ለመፍጠር የሚረዳ የኢ-ለርኒንግ ሲስተም ወደ ስራ መግባቱን አስታውቀዋል።
የመንግስት ግዥ አገልግሎት ዋና ዳይሬክተር አቶ አስማረ ይገዙ በበኩላችው፥የንብረት ማስወገድ ስራ ተቋማት በሚያቀርቡት የይወገድልኝ ጥያቄ ላይ መመስረቱ ውጤታማ አለመሆኑ ተለይቷል ብለዋል።
በዚህም በበጀት ዓመቱ በአገር አቀፍ ደረጃ በርካታ የሚወገዱ ንብረቶች ያላቸውን የተመረጡ ተቋማትን በመጎብኘትና ንቅናቄ በማድረግ የተሻለ አፈጻጸም መመዝገቡን ዋና ዳይሬክተሩ ተናግረዋል።
በበጀት አመቱ አስር ወራት የተከናወነው የንብረት ማስወገድ ስራ አፈጻጸም ከባለፈው አመት ተመሳሳይ ወቅት ጋር ሲነጻጸር ከ56 በመቶ በላይ ብልጫ እንዳለው ነው የጠቀሱት።
ይህም የመንግስትን ንብረት ከብክነት ከማዳንና ገቢ ከመጨመር አኳያ ከፍተኛ ውጤት ማስገኘቱን ዋና ዳይሬክተሩ አስታውቀዋል።
ባለፉት አስር ወራት በማዕቀፍ ስምምነት ከ2 ነጥብ 4 ቢሊዮን ብር በላይ ግምት ያላቸው የጋራ መገልገያዎች እና 9 ነጥብ 3 ቢሊየን ብር የሚገመቱ የኤሌክትሪክ ተሽከርካሪዎች ግዢ መፈጸሙንም ገልጸዋል።
ዕቃዎቹ ሙሉ በሙሉ በኤሌክትሮኒክስ ግዥ ስርዓት ማለፋቸውን ገልጸው፥ይህም ፍትሃዊ፣ተወዳዳሪና ግልጽ አሰራር መፍጠር ከመቻሉ ባለፈ ህገ ወጥነትን ማስቀረቱን ተናግረዋል።
ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...
Sep 4, 2026
አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...
Sep 3, 2026
ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...
Aug 12, 2026
አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...
Aug 12, 2026