የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

መንግሥት ለያዘው የማዕድን ልማት መጠናከር ዩኒቨርሲቲዎች በጥናትና ምርምር ሊደግፉ እንደሚገባ ተመላከተ

Nov 10, 2025

IDOPRESS

🔇Unmute

አዳማ፤ ጥቅምት 30/2018(ኢዜአ)፦ መንግስት የማዕድን ልማትን ለማጠናከር የሰጠው ትኩረት ለሀገራዊ ዕድገት መፋጠን ፋይዳው የጎላ በመሆኑ በጥናትና ምርምር መደገፍ እንደሚገባ በአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የሚሰሩ ምሁራን ገለጹ።

በዩኒቨርቲው የተፈጥሮ ሣይንስ ኮሌጅ የአፕላይድ ጂኦሎጂ ትምህርት ክፍል ኃላፊና ተመራማሪ አስፋው ኤርበሎ(ዶ/ር) ለኢዜአ እንደገለጹት መንግስት የማዕድን ልማትን እንደ አንድ ዋነኛ የዕድገት ምንጭ አድርጎ መንቀሳቀሱ የሚደገፍ ነው።

ዘርፉን በቴክኖሎጂ ለማጠናከር በሚሰራው ሥራ ከፍተኛ የትምህርት ተቋማት በጥናትና ምርምር ሥራዎች ሊደግፉ ይገባል ብለዋል።

የማዕድን ልማት በተፈጥሮ ውስብስብ ሂደቶች እንዳሉትና ችግሮች ሊገጥሙ እንደሚችሉ ጠቅሰው፣ ይህንንም ለመፍታት በየጊዜው ጥናትና ምርምር ማከናወን እንደሚገባ ገልጸዋል።

ለዚህም የዩኒቨርሲቲ ምሁራን ጥናትና ምርምር በማድረግ ለማዕድን ልማቱ ስኬታማነት የራሳችንን አስተዋጽኦ ልናደርግ ይገባል ብለዋል።

በተለይ በከፍተኛ የትምህርት ተቋማት ጠንካራ ቤተ ሙከራ በማደራጀት ዘርፉን የሚያሳድጉ የጥናትና ምርምር ሥራዎችን በማካሄድ መንግስትን ማገዝ እንደሚገባ አመልክተዋል።

በዚህ ረገድ የአዳማ ሣይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ ሥነ ምህዳር ሣይንስ ክፍል የጎላ አስተዋጽኦ እንዲኖረው በዘመናዊ ላቦራቶሪ ለማጠናከር እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል።

ለአብነት የኤሌክትሪክ መኪናዎች እንዲሁም በውሃና በንፋስ ኃይል የሚሰሩ የሃይል ማመንጫ ማሽነሪዎች የሚሰሩት ማዕድናትን በመጠቀም እንደሆነ ጠቅሰዋል።

በመሆኑም የከፍተኛ ትምህርት ተቋማት ተመራማሪዎችና መምህራን መንግሥት ለያዘው የማዕድን ልማት ግብዓት የሚሆኑ ጥናትና ምርምሮችን በማድረግ ማገዝ እንዳለባቸው አስገንዝበዋል።

የአዳማ ሳይንስና ቴክኖሎጂ ዩኒቨርሲቲ የጂኦሎጂ ትምህርት ክፍልም በአዳማ ከተማ ዙሪያ ባሉ የማዕድን አይነቶች ላይ ካለፈው ዓመት ጀምሮ ጥናትና ምርምር እያከናወነ መሆኑን ተናግረዋል።

በተለይ ከአዳማ ከተማ ዕድገት ጋር ተያይዞ በአካባቢው ከፍተኛ የግንባታ ግብዓት ፍላጎት እንዳለ የጠቀሱት ኃላፊው፣ ይህንን ፍላጎት ለማርካትና ሀብቱን በሥርዓት ለማስተዳደር ጥናቱ ጠቀሜታ እንደሚኖረው አስታውቀዋል።

በዩኒቨርሰቲው የማዕድን ኢንጂነሪንግ ጂኦፊዚክስ መምህር አብደላ በሪሶ በበኩላቸው እንዳሉት፣ ዩኒቨርሲቲው ብቃት ያላቸውን የሥነ ምድር ሳይንስ ምሁራንና ተመራማሪዎችን ከማፍራት ጎን ለጎን እንደሀገር ትኩረት ለተሰጠው የማዕድን ልማት አጋዥ ለሆኑ ጥናትና ምርምሮች ትኩረት ሰጥቷል።

መንግሥት በማዕድን ዘርፍ የያዘው አቅጣጫ የሀገሪቱን ዘላቂ የልማት ግቦች ለማሳካት ወሳኝ በመሆኑ ምሁራን ሙያዊ አስተዋጽኦ በማድረግ ልንደግፍ ይገባል ብለዋል።

የማዕድን ልማት በባህሪው ሰፊ ሀብትና እውቀት የሚጠይቅ በመሆኑ የባለድርሻ አካላት የተቀናጀ ርብርብ ወሳኝ መሆኑንም አመልክተዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026