የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የኮደርስ ስልጠና በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ነው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

‎‎‎‎‎‎‎ዲላ፤ ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የኮደርስ ስልጠና ጥልቅ እውቀት በማስጨበጥ በዘርፉ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል ነው ሲሉ የኮደርስ ሰልጣኞች ተናገሩ።

በጌዴኦ ዞንና ዲላ ከተማ የስልጠናው ተሳታፊዎችና አስተያየታቸውን ለኢዜአ የሰጡ ባለሙያዎች፤የኮደርስ ስልጠና ጥልቅ እውቀት በማስጨበጥ በዘርፉ በዓለም ደረጃ ተወዳዳሪ ለመሆን የሚያስችል መሆኑን ተናግረዋል።

የስልጠና ዕድሉ ማንም ሊያመልጠው አይገባም ያሉት ሰልጣኞቹ፣ ስልጠናው ያላቸውን የቴክኖሎጂ እውቀት ከማሳደግ ባለፈ ስራቸውን በውጤታማነት ለማከናወን ጉልህ ፋይዳ እንዳለው ገልጸዋል።


በዞኑ የፋይናንስና ፕላን ልማት መምሪያ ባለሙያ አቶ ዳዊት ተፈራ፤ ከዚህ ቀደም በኢትዮ ኮደርስ በዳታ ፕሮግራሚንግ፣ በሰው ሰራሽ አስተውሎትና በአንድሮይድ ዘርፎች የወሰዱት ስልጠና በዘርፉ የነበራቸውን ክህሎት እንዳሳደገው ተናግረዋል፡፡

በተለይ የዳታ ፕሮግራሚንግ ስልጠና ከተሰማሩበት የሥራ መስክ ጋር በእጅጉ የተቆራኘ በመሆኑ የመፈጸም አቅማቸውን እንዳሻሻለው ነው የገለጹት።


በአሁኑ ወቅትም በፕሮግራሚንግ ዘርፍ ተጨማሪ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑን ጠቁመው፣ ይህም እውቀታቸውን በማስፋት ተወዳዳሪነታቸውን እንደሚያሳድገው ተናግረዋል።

ከዲጂታል ዓለም ፈጣን እድገት ጋር አብሮ ለመጓዝ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰድ ጠቀሜታ አለው ያሉት የዞኑ ሥራና ክህሎት መምሪያ ባለሙያ አቶ ሰለሞን አበበ ናቸው።


ከዚህ ቀደም በዳታ ፕሮግራሚንግ ዘርፍ የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና መውሰዳቸው በማይክሮ ሶፍት ሁሉም መተግበሪያዎች ላይ ያላቸውን ክህሎት አሳድጎላቸዋል።

በተለይ መረጃ አያያዛቸውን በማዘመን ምቹ የሥራ አካባቢ መፍጠር መቻላቸውን ጠቅሰው በሌሎች ዘርፎችም አቅማቸውን ለማሳደግ የኮደርስ ስልጠና መጀመራቸውን ገልጸዋል።

ስልጠናው ለቴክኖሎጂ ያለኝን ዝንባሌ ለማጎልበት መልካም አጋጣሚ ፈጥሮልኛል ያለችው ደግሞ የዲላ 2ኛ ደረጃ ትምህርት ቤት የ12 ክፍል ተማሪ መድሀኒት ተገኝ ናት።


የጌዴኦ ዞን ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ አቶ ደረጀ ሾንጣ እንዳሉት፤ በዞኑ ከ16 ሺህ በላይ ዜጎች ስልጠናውን ተከታትለው በማጠናቀቅ የምስክር ወረቀት አግኝተዋል፡፡

የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና በዘርፉ ብቁና ተወዳዳሪ ዜጋ ለማፍራት የሚደረገውን ጥረት እያገዘ መሆኑን ገልጸው፣ በአሁኑ ወቅትም በ80 ማዕከላት በዘመቻ እየተሰጠ ባለው ስልጠናም ከ22 ሺህ በላይ ዜጎች እየተሳተፉ መሆናቸውን ተናግረዋል።


‎በዲላ ከተማ እየተሰጠ ያለውን ስልጠና የመንግስት ሠራተኞችና አመራሮች፣ መምህራንና ተማሪዎች እየወሰዱ መሆኑን የገለጹት ደግሞ የዲላ ከተማ አስተዳደር ኢኖቬሽንና ቴክኖሎጂ መምሪያ ኃላፊ ወይዘሮ ፀሐይ ቦጋለ ናቸው።

በዞኑና በዲላ ከተማ አስተዳደር በአንድ ጀንበር ንቅናቄ ከ34 ሺህ በላይ ዜጎች በ93 ማዕከላት የኢትዮ ኮደርስ ስልጠና እየወሰዱ መሆኑ ተመላክቷል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026