የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ፕሮጀክት በፍጥነት ሊጠናቀቅ ይገባል-ቋሚ ኮሚቴው

Jan 23, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

አዲስ አበባ፤ጥር 13/2018(ኢዜአ)፦ የአዳማ-አዋሽ ምዕራፍ አንድ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ለሀገሪቱ ንግድ መሳለጥ ከፍተኛ ፋይዳ ስላለው በፍጥነት ሊጠናቀቅ እንደሚገባ በሕዝብ ተወካዮች ምክር ቤት የከተማ፣ መሠረተ ልማትና ትራንስፖርት ጉዳዮች ቋሚ ኮሚቴ አሳሰበ።

የቋሚ ኮሚቴው አባላት የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ግንባታ አጠቃላይ የሥራ እንቅስቃሴ ላይ የመስክ ምልከታ አካሂደዋል።


የኢትዮጵያ መንገዶች አስተዳደር ዋና ዳይሬክተር ኢንጂነር መሐመድ አብዱራህማን በዚሁ ወቅት እንደገለጹት፤ የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ምዕራፍ አንድ ፕሮጀክት 61 ነጥብ 5 ኪሎ ሜትር ርዝማኔ አለው።

ግንባታው በኢትዮጵያ መንግሥት እና በአፍሪካ ልማት ባንክ ድጋፍ እየተከናወነ እንደሚገኝ የጠቀሱት ዋና ዳይሬክተሩ፤ በአሁኑ ወቅት በ40 ኪሎ ሜትር በሚጠጋው የመንገድ ክፍል ላይ የሁለተኛ ዙር አስፋልት ንጣፍ ሥራ መጠናቀቁን አብራርተዋል፡፡


ፕሮጀክቱ ሲጠናቀቅም በአንድ ጊዜ አራት ተሽከርካሪዎችን የማስተናገድ አቅም ይኖረዋል ብለዋል።

ግንባታው እንደ ወሰን ማስከበርና የካሳ ክፍያ ያሉ ተግዳሮቶች ገጥመውት የነበረ መሆኑን ጠቅሰው፤ ተቋሙ አሁን ላይ እነዚህን በማለፍ ፕሮጀክቱን ለማጠናቀቅ እየተሰራ መሆኑን ተናግረዋል፡፡

ፕሮጀክቱን በፍጥነትና በጥራት ለማጠናቀቅ በልዩ ትኩረት እየተሠራ ይገኛል ብለዋል፡፡

የቋሚ ኮሚቴው አባላት በበኩላቸው ግንባታው ከተጀመረ ዓመታት ቢቆጠሩም በተለያዩ ምክንያቶች መዘግየቱን መታዘባቸውን ገልጸዋል።

ይሁን እንጂ ችግሮችን በመቋቋም ለሀገር ኢኮኖሚ ዋልታ የሆነውን የመንገድ ፕሮጀክት ሥራን ዘመናዊ ቴክኖሎጂዎችን በመጠቀም ለማፋጠን እየተከናወኑ ያሉ አበረታች ተግባራትን አጠናክሮ ማስቀጠል እንደሚገባ አሳስበዋል።


የቋሚ ኮሚቴው ሰብሳቢ ፕሮፌሰር መሐመድ አብዶ፤ የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ መጠናቀቅ የሀገሪቱን የገቢና ወጪ ንግድ ዘርፍ ለማሳደግ ሚናው የጎላ ነው ብለዋል።

በመሆኑም አስተዳደሩ ግንባታውን በጥራትና በፍጥነት ሊያጠናቅቅ እንደሚገባ አሳስበው፤ ቋሚ ኮሚቴው ለሥራው ማነቆ የሆኑ ችግሮችን ለመፍታት የሚጠበቅበትን ግዴታ ለመወጣት ዝግጁ መሆኑን አረጋግጠዋል።

የአዳማ-አዋሽ የፍጥነት መንገድ ግንባታ ፕሮጀክት የኢትዮጵያ-ጅቡቲ የትራንስፖርት ኮሪደር አካል የሆነው የአዳማ-አዋሽ-መኢሶ-ድሬዳዋ የፍጥነት መንገድ ኮሪደር ፕሮጀክት አካል መሆኑን ከተቋሙ የተገኘው መረጃ ያመለክታል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026