የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ
ግንኙነት
ፈልግ
ህይወት እና ጉዞ

የቡና ጥራትን በማስጠበቅ ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ የማሳደግ ስራ እየተከናወነ ነው

Feb 13, 2026

IDOPRESS

🔇Unmute

ጊምቢ፤ የካቲት 5/2018 (ኢዜአ)፡-የቡና ጥራትን በማስጠበቅና ግብይትን በማሳለጥ ከዘርፉ የሚገኘውን የውጭ ምንዛሪ ለማሳደግ የተለያዩ ተግባራት እየተከናወኑ መሆኑን የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለስልጣን አስታወቀ።

የተለያዩ ባለድርሻ አካላት የተሳተፉበት የቡና ፈስቲቫል በጊምቢ ከተማ የተካሄደ ሲሆን ባለሥልጣኑ የቡና ጣእምና ጥራት ማረጋገጫ ማዕከልንም ዛሬ በይፋ ስራ አስጀምሯል።


በፌስቲቫሉ ላይ የተገኙት የኢትዮጵያ ቡናና ሻይ ባለሥልጣን መሠረታዊ አገልግሎት ስራ አስፈፃሚ አቶ ብርሃኑ ቆርቾ እንዳሉት፤ የቡና ጥራትን በማስጠበቅና የግብይት ሰንሰለቱን በማሳለጥ የቡና አምራቹን ተጠቃሚነት ለማረጋገጥ እየተሰራ ነው።

ለዚህም በቡና አምራች አካባቢዎች የቡና ጥራትና የጣእም ደረጃ የሚያረጋግጡ ማዕከላት በቅርበት እየተከፈቱ መሆኑን ጠቁመው ይህም ቡና አምራቹ አርሶ አደርና በዘርፉ የተሰማሩ ነጋዴዎች ለጥራት ትኩረት እንዲሰጡ ያነሳሳል ብለዋል።

የቡና ጥራትን በዘላቂነት ለማስጠበቅ መንግስት የተለያዩ ድጋፎች ሲያደርግ መቆየቱን ገልጸዋል።

እንዲሁም አርሶ አደሮች ጥራቱን የጠበቀ የቡና ምርት እንዲሰበስቡም ከባለድርሻ አካላት ጋር በመተባበር ስልጠና መሰጠቱን ተናግረዋል።

ይህም የቡና ምርትና ምርታማነትን በማሳደግ ሀገራችን ከዘርፉ የምታገኘውን የውጭ ምንዛሪ እያሳደገው እንደሚገኝ አስታውቀዋል።

የምእራብ ወለጋ ዞን ዋና አስተዳዳሪ አቶ ተሊላ ተረፈ በበኩላቸው፤ በዞኑ ቡናን በብዛትና በጥራት በማምረት ለማዕከላዊ ገበያ የማቅረብ ስራ በትኩረት እየተከናወነ መሆኑን ገልጸዋል።

ዛሬ የቡና ጣእምና ጥራት ማረጋገጫ ማዕከል ወደ ስራ መግባቱም ይህንን ስራ ለማጠናከር እና የዞኑ ቡና አምራች አርሶ አደርን የረጅም አመታት ጥያቄ የሚፈታ መሆኑን ገልጸዋል።

የዞኑን የቡና ምርት ጥራት ደረጃን ለማሻሻልም ቡና አምራች አርሶ አደሮች፣ ነጋዴዎች፣ አመራሮች እና ባለሙያዎችን ያሳተፈ ውይይት መካሄዱን ገልጸዋል።

የኢትዮጵያ ፕሬስ ድርጅት - የኢትዮጵያ ድምጽ

የኢትዮጵያ ዜና አገልግሎት ወቅታዊ፣ ትክክለኛ እና አጠቃላይ የዜና ዘገባዎችን ለማቅረብ የሚሰራ የኢትዮጵያ የዜና ወኪል ነው። ጠቃሚ የሀገር ውስጥ እና አለምአቀፍ ሁነቶችን እንዘግባለን፣ ሀገራዊ ፖሊሲዎችን እና ማህበራዊ ለውጦችን በጥልቀት በመመርመር ለህዝብ፣ ለመንግስት ኤጀንሲዎች፣ ለንግድ ድርጅቶች እና ለአለም አቀፉ ማህበረሰብ ታማኝ የዜና ምንጭ እናቀርባለን። ጋዜጠኞቻችን በአገር ውስጥ እና በውጭ አገር አዳዲስ ዜናዎች እና መረጃዎች በተቻለ ፍጥነት እንዲደርሱ እና ግልጽነትን እና የህዝብ ተሳትፎን ለማስተዋወቅ ነው.

መግለጫ

በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መጥቷል

ጋምቤላ፤ ነሐሴ 28/2018 (ኢዜአ)፡- በጋምቤላ ክልል ተግባራዊ የተደረገው የሩዝ ልማት ኢኒሼቲቭ ውጤታማ እየሆነ መምጣቱን የክልሉ እርሻና ተፈጥሮ ሃብት ልማት...

Sep 4, 2026

በክልሉ ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ ይቀጥላል -ርዕሰ መስተዳድር አሻደሊ ሀሰን

አሶሳ፤ ነሐሴ 27/2018 (ኢዜአ)፡- በቤኒሻንጉል ጉሙዝ ክልል ኢንዱስትሪዎችን በማስፋፋት ተኪ ምርቶችን የማምረት ስራ ተጠናክሮ እንደሚቀጥል የክልሉ ርዕሰ ...

Sep 3, 2026

በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በሥራ ዕድል ፈጠራ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት ተገኝቷል

ሆሳዕና፤ ነሀሴ 5/2018 (ኢዜአ)፡-በማዕከላዊ ኢትዮጵያ ክልል በተጠናቀቀው በጀት ዓመት ዜጎችን በሥራ ዕድል ተጠቃሚ ለማድረግ በተከናወኑ ሥራዎች ውጤት መመዝገ...

Aug 12, 2026

በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው ይገባል

አዲስ አበባ፤ነሐሴ 5/2018 (ኢዜአ)፦የመንግሥት በሙስናና ሕገ ወጥ ድርጊት የተሰማሩ አካላትን በሕግ ተጠያቂ የማድረግ ርምጃ ቀጣይነት ሊኖረው እንደሚገባ ኢዜአ...

Aug 12, 2026